በመላው አለም የሚገኙ መንግስታት፣ ኩባንያዎችና ግለሰቦች ባለፈው የፈረንጆች አመት 24 ትሪሊዮን ዶላር መበደራቸውንና አለማቀፉ አጠቃላይ ብድር በአመቱ መጨረሻ 281 ትሪሊዮን ዶላር መድረሱን ብሉምበርግ ከሰሞኑ ባወጣው ዘገባ አስነብቧል፡፡
ኢንስቲቲዩት ኦፍ ኢንተርናሽናል ፋይናንስ የተባለው አለማቀፍ ተቋም ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፤ 281 ትሪሊዮን ዶላር የደረሰው አለማቀፉ አጠቃላይ ብድር፣ በታሪክ ከፍተኛው ሲሆን ገንዘቡ ከአለማቀፉ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት ከ355 በመቶ በላይ እንደሚሆንም ለማወቅ ተችሏል፡፡
ከፍተኛ የበጀት ጉድለት የገጠማቸው የአለማችን አገራት፣ በአዲሱ የፈረንጆች አመት 2021፣ ተጨማሪ 10 ትሪሊዮን ዶላር ያህል ይበደራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ዘገባው አመልክቷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ