Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Print this page
Saturday, 18 August 2012 12:15

ለኑሮ አመቺና አስቸጋሪ ከተሞች ይፋ ተደረጉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የአውስትራሊያዋ ሜልቦርን ቀዳሚ ደረጃ ይዛለች

መቀመጫውን እንግሊዝ ያደረገውን “ኢኮኖሚስት ኢንተለጀንስ ዩኒት” በአለም ላይ የሚገኙ አንድ መቶ አርባ ከተሞች ላይ ባደረገው የኑሮ አመቺነት ጥናት የአውስትራሊያዋ ሜልቦርን እጅግ ለኑሮ አመቺ ከሆኑ የዓለም ከተሞች ቀዳሚነቱን ስትይዝ፤ የባንግላዴሽ ዋና ከተማ  ዳካ ለኑሮ የማትመች የመጨረሻዋ አስቸጋሪ ከተማ ተብላለች፡፡ የከተሞቹን ደረጃ ለማውጣት የተለያዩ መስፈርቶች የተቀመጡ ሲሆን መረጋጋት (ከወንጀል አንፃር)፣ የጤና አጠባበቅ፣ ባህል እና ከባቢያዊ ሁኔታ፤ ትምህርት እና መሠረተ ልማት በዋና መስፈርትነት ተወስደዋል፡፡

 

በከተሞቹ ላይ በተካሄደው ጥናት መሠረት፤ ለኑሮ አመቺ ናቸው ተብለው ከተመረጡ አስር አገሮች ውስጥ ከአውስትራሊያ ሜልቦርን፣ አዴልአይሌ፣ ሲድኒ እና ፐርዝ ሲገኙበት፤ ከካናዳ ቫንኩቨር፣ ቶሮንቶ እና ካልጋሪ ተመርጠዋል፡፡ የአውሮፓ ከተሞቹ ቪየና እና ሔልሲንኪ እንዲሁም የኒውዚላንዷ ኦክላንድም በዚሁ ምድብ ተካተዋል - ለኑሮ አመቺ ከተማ በመሆን፡፡

የመካከለኛው ምስራቅ እና የሠሜን አፍሪካ አገራት (ከተሞች) ለኑሮ ከማይመቹት መካከል የተመደቡ ሲሆን ካቡል፣ ባግዳድ እና ሞቃዲሾ ግን በጥናቱ አልተካተቱም ተብሏል፡፡ የሶሪያ ዋና ከተማ ደማስቆስ ደግሞ የአንድ መቶ ሰላሳኛ ደረጃን አግኝታለች - ከ140 ከተሞች፡፡ ከእንግሊዝ ከተሞች ለኑሮ አመቺ ተብላ ቀዳሚውን ሥፍራ የያዘችው ማንቸስተር ስትሆን  ሀምሳ አንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡ ኦሎምፒክን በተሳካ ሁኔታ ያስተናገደችው ለንደን ደግሞ በሀዋሳ አምስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች - በኑሮ አመቺነት፡፡

ጥናቱ ለኑሮ የማይመቹ በሚል ከለያቸው ከተሞች ውስጥ ቴህራን፣ ትሪፖሊ፣ ካራቺ፣ አልጀርስ እና ሀራሬ የሚገኙበት ሲሆን የባንግላዴሽ ዋና ከተማ ዳካ ግን ለኑሮ እጅግ በጣም የማትመች ተብላለች፡፡

ከተማዋ ጥሩ ጎኖች እንዳሏት የጠቆመው ሪፖርቱ፤ የኢኮኖሚዋ ጥንካሬ እየተሻሻለ መምጣቱን፣ የትምህርት ዕድሎችን እያስፋፋች እንዲሁም የባህል ትስስሯም እጅግ ጥሩ እንደሆነ ቢጠቅስም በየአመቱ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሚጨምረው የህዝብ ብዛቷ የአራት መቶ አመት እድሜ ያላትን ዳካ የተጨናነቀች ከተማ እንድትሆን አድርጓታል ብሏል፡፡

 

 

Read 66877 times Last modified on Saturday, 18 August 2012 12:22

Latest from