Saturday, 27 March 2021 12:35

አዳኞቹና ድቡ

Written by 
Rate this item
(7 votes)

   ከእለታት አንድ ቀን ፤ አዳኖች ጫካው ውስጥ ሁለት ወዳሉ ድቦች ያገኛሉ። አንደኛው አዳኝ ፈጥኖ ወደ አንድ ዛፍ ላይ ወጣ። ሁለተኛው ድብ መንገዱ ላይ ተዝለፍልፎ ወደቀ።
ድቡ ጠጋ ብሎ አሸተተው፡፡ አሸተተውና ትቶት ሄደ፡፡
ዛፍ ላይ የወጣው ጓደኛው ወርዶ ወደ ወደቀው ጓደኛው መጣና፤
“ለመሆኑ ድቡ ምን አለህ?” አለና ጠየቀው።”
ጓደኝየውም፤
“ድቡ ምን አለኝ መሰለህ ሁለተኛ እንደዚህ ያለ ጓደኛ መቼም እንዳይኖርህ ተጠንቅቆ” አለው። ጓደኝየውም፣
“ምነው እኔንም ይህንኑ ዓይነት ምክር በመከረኝ” ብሎ ፀፀቱን ገለፁለት።
*   *   *
የጥሩና ፅኑ ጓደኝነት ፍሬ ነገር ልባዊ! ወዳጅነት። የሁሉም ወዳጅነት ማሳኪያው ፍቅር፣ እውነትና ታማኝነት ናቸው። ማህበረሰባችን እነዚህን እሴቶች እያለማ ወደፊት እንዲጓዝ ምኞታችን ከፍ ያለ ነው። ከመመንደግ ይቀድማል ማደግ! ከማደግ በፊት የማያዳግም ህልም! ይህን ህልም መስመር ማሲያዝ ለብቻው ከባድ ትግል ነው። ሁሌም አንድን ትግል ማሸነፍ የሚቻለው በማያቋርጥ እንቅስቃሴ ነው።
የማያቋርጠውን  እንቅስቃሴ መልክ ለማስያዝ ብርቱ የማስተባበር ጥንቃቄን ይጠይቃል።
የተገዢዎቹን መላና ትእግስት የሚቃኘው የገዢዎች ጠቢብነትና  ብስለት ነው፡፡ ያም ሆኖ መንገዱ ሁሉ ጠመዝማዛ እንጂ ሁሉም ቀጥ ያለና ሊሾ አይደለም። መንገዱን መልመድንና መጎረባበጥን ግድ ይላል!
በእርግጥ መንገዱ በሁለንተናዊ መንፈሱ ችግር በችግር ይሁን ማስታችን አይደለም።
“አልኩሃ ምን ትሆን
*   *   *
አልኩሃ ምን ትሆን
እኔም እናትህ ነኝ
“አንተም ልጄ ብትሆን” ማለታችን እንጂ።
እድላችን እራሳችን እናንብብ!!  እራሳችን  እንገንዘብ! መቼም ይሁን መቼም መማር አይቆምም! ዋናው ቁም ነገርም ይሄው ነው።
አንዳንድ ሁኔታ መቼም ላይለቀን የተማማልን ይመስላል- የሀገራችን ነባራዊና ህሊናዊ ሁኔታ   ( subjective and objective)  የግዱን የሚያስፈልገንን ያስደርገናል።
አሁን ያለን መንግስት የእጀርባ እንጂ የነፃ አስተሳሰብ ሀሳብ ላይ ያተኮረ እየሆነ እንዳልሆነ አውቀናል- ገምተናል- አስልተናል….
ባንድ ልብ ፕሮቴስታንት
ባንድ ልብ  ሚሊቴሪ ነን
ባንድ ልብ- ናሽናሊስት (ብሔርተኛ) ነን!
ባንድ ልብ  አገር ወዳድ ነን!
ኢትዮጵያ የማንኛውንም አገር አካሄድ ያለመቀበል መብት አላት፤ ሉዐላዊት አገር ናትና!
እንደምታሸንፍ እናውቃለን! ምክንያቱም ታሪኳ፤ ፖለቲካዊ፣ ጂኦግራፊዊ፣ የማይሸነፍ ጀግኖች ልጆቿ ናቸው። ነፍሳቸው ደማቸውን  ከፍለውታል- ልብ ስላላቸው ልብ  ይሰውላቱታል፡፡ ሰው ስላላቸው ሰውነታቸውን ያሳዩታል፡፡ ልጆቿን በዚሁ ፍሬ ታፈራለች ዕልፍ አዕላፍ ታመርታለች፡፡ “ይህችው ናት አገርህ! ሀገርህ ናት በቃ!አብረህ አንቀላፋ ወይ አብረሀት ንቃ ያልነው” ለዚህ ነው፡፡


Read 13208 times