Saturday, 24 April 2021 12:22

በአገራችን 10ኛው የፓርኪንሰ ቀን ተከበረ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 በአገራችን ለ10ኛ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ዳግም ለ24ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የፓርኪንሰን ቀን ከትናንት በስቲያ ተከበረ፡፡ “ትኩረት ለፓርኪንሰን ሕሙማን” በሚል መሪ ቃል በተከበረው በዚህ በዓል ላይ የፓርኪንሰን ህሙማን የሚገጥማቸውን የጤና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች የሚዳስሱ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች ቀርበዋል፡፡
በፕሮግራም ላይ ንግግር ያደረጉት የፓርኪንሰን ህሙማን መርጃ ተቋም መስራች ወ/ሮ ክበረ ከበደ እንደተናገሩት፤ የፓርኪንሰን በሽታ ሊድን የማይችልና በየጊዜው እየተባበሰ የሚሄድ መሆኑን አስታውሰው፤ ህሙማኑ ለከፋ ችግርና የህመም ስቃይ እንዳይዳረጉ ለማድረግ የሚያስችሉ መድሀኒቶች ማግኘት ይኖርባቸዋል፡፡
በአገራችን ግን ህሙማኑ በመድሀኒት እጦት ሳቢያ እጅግ ለከፋ ስቃይና ህመም ሲዳረጉ ማየት የተለመደ ሆኗል ብለዋል፡፡ መንግስትና ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ህሙማን መድሀኒት ማግኘት የሚችሉበት ሁኔታ ላይ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል  ሲሉም ተናግረዋል።  
ህብረተሰቡ ለፓርኪንሰን ህሙማን ተገቢውን ጥበቃና እንክብካቤ በማድረግ ህሙማኑ ከሚያጋጥማቸው ማህበራዊ መገለልና ችግር ሊታደጓቸው ይገባል ብለዋል።


Read 7872 times