Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 01 September 2012 11:45

ንጉሥም እንደ ሰው!

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ያው ሰው - ኖሮ ኖሮ

ኑሮን ዞሮ - ዞሮ

ደፈና ሕይወቱን

ወይ ኢምንት ጉልበቱን

በጊዜ እየኖረ - ጊዜውን ጠብቆ - በጊዜ እየሞተ

ስንቱ በሞት ሰፈር - በዛ በረከተ

ሞት ላይሞት ሰው ሞተ

አፈረ - ባከነ - ባዘተ - ቃተተ፡፡

ይህ ነበር ሂደቱ - የፍጥረታት ምሱ

ከአፈርም ወደ አፈር - አፈር የመልበሱ!

ዋ በዚች ፍልሰታ - በክረምቱ ሰማይ

በጊዜ የሞተ - ሞቶ በጊዜው ላይ

ለካ እጠብቅ ነበር አንድ ጀግና እስከማይ - አንድ ሰ’ማት እስካይ፡፡

እኮ ማነህ አንተ…

እንደ ልጅ ያልኖርከው - ዘለህ ያልጠገብከው

የፍቅር ቄጠማ - ያልቀነጣጠስከው

ኮበሌ ተብለህ - በወግ ያልተዳርከው…?

እኮ ማነህ አንተ…

በአረር ጫጫታ - በመድፍ ጉምጉምታ

በጥይት እሩምታ - በባሩዱ ሽታ

በዚያ ሁሉ መዓት…

ግብግብ የያዝከው - ከኪታብ ጋጋታ

ራስክን የቀበርከው - በፊደል ገበታ

ሽሪታ የወጣኸው - ዕውቀትን ሸመታ…?

እኮ ማነህ አንተ…?

ተስፋይቱን ምድር - ከሰው ሁላ ቀድመህ

ሩቅ ልምላሜን - ከሩቅ አስተውለህ

ማርና ወተቷን - በነፍስ አጣጥመህ

አንድ ስንዝር ቢጤ - ርቀት እንደቀረህ

በግሮችህ ሳትረግጣት - መንገድ የወደቅኸው

ሳትደርስ የቀረኸው - ቀድመህ የገባኸው…?

እኮ ማነህ አንተ…?

ላጠናህ ብሞክር - አንዴ እንኳን እንደ ሰው

ልክ እንደ ሰፊው ሕዝብ - ብዙ ህልም እንዳለው

እንደ ራስ ወዳዱም - ለራሱ እንደኖረው

ውልደት ሞትክን እንጂ - መኖርን ላጣኸው

ሳ’ትኖር በመሞትህ - ኑሮዬን አፈርኩት

ሞተህ በመኖርህ - ዋ ሞቴን ፈራሁት፡፡

እኮ ማነህ አንተ… ሞተሃል የሚሉኝ?

እኮ ማነኝ እኔ…የምለው ቋሚ ነኝ?

ቢሰንድቅ ዋልታችን - ቢሰየም አምባችን

ቢነገር ውላችን - ቅሪት መጠሪያችን

እኔ ነኝ የኖርኩት - አንተ ሞተህ ስትኖር

እኔ ነኝ የሞትኩት - በሞትህ ስትኖር፡፡

ጥላሁን አ. (ወለላው)

ለ - መለስ ዜናዊ አስረስ

 

 

Read 2301 times Last modified on Saturday, 01 September 2012 11:50