Sunday, 11 July 2021 17:51

የሞባይል ጨረሮች ለበሽታ እንደሚያጋልጡ አንድ ጥናት ጠቆመ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ከሞባይል ስልኮች የሚወጡ ጨረሮች ለአንጎል ካንሰር፣ ለነርቭ ህመሞችንና የስነተዋልዶ ጤና እክሎችን ጨምሮ ለተለያዩ በሽታዎች የማጋለጥ ዕድላቸው ከፍ ያለ መሆኑን ከሰሞኑ የወጣ አንድ ጥናት አመልክቷል፡፡
የበርክሌይ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ይፋ ያደረጉት የጥናት ውጤት እንደሚለው ለ10 ተከታታይ አመታት በየቀኑ ለ17 ደቂቃ ያህል ሞባይል ስልኮችን መጠቀም፣ ለአንጎል ካንሰር የመጋለጥ እድልን በ60 በመቶ ያህል እንደሚጨምር ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
ዋይፋይ እና ብሉቱዝ አብርቶ ወይም ክፍት አድርጎ በብዛት ሞባይል መጠቀም ከአንጎል ካንሰር በተጨማሪ ለነርቭ ህመሞችና ለስነተዋልዶ ችግሮች እንደሚያጋልጥ የጠቆመው የጥናት ውጤቱ፣ ሞባይሎችን ከሰውነትና ከጭንቅላት በ10 ኢንች ያህል ማራቅ ለተጠቀሱት በሽታዎች ከመጋለጥ እንደሚከላከልም ገልጧል፡፡

Read 1351 times