አንድ የወንጀል ድርጊትን ለመመርመር በሩስያ ገጠራማ አካባቢ ወደሚገኝ ቅንጡ መኖሪያ ቤት ያመሩ የአገሪቱ ፖሊሶች፣ እጅግ ውድ በሆነ ወርቅ የተለበጠ የሙሰኛ ፖሊሶች መጸዳጃ ቤት ማግኘታቸው ተነግሯል፡፡
ስታቭሮፑል በተባለው የአገሪቱ አካባቢ የትራፊክ ፖሊስ ሃላፊ የሆኑ አንድ ኮሎኔል ሙስና በመቀበል ሃሰተኛ የይለፍ ፈቃድ በመስጠት የፈጸሙትን ወንጀል ለማጣራት ወደ ስፍራው ያመሩ ፖሊሶች፣ በቅንጡው ቤት ውስጥ በወርቅ የተለበጠውን መጸዳጃ ቤት ማግኘታቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡
መርማሪዎቹ በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብና እጅግ ውድ የቅንጦት መኪኖችን ጭምር ማግኘታቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ ኮሎኔሉና አምስት ግብረ አበሮቻቸው ለአመታት በሙስና ከ225 ሺህ ዶላር በላይ ማካበታቸውን ለማረጋገጥ መቻላቸውን እንዳስታወቁም ገልጧል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል