Sunday, 22 August 2021 12:46

“የአዲስ ዓመት ተስፋዎቻችን ለሀገራችን” የመፅሐፍት አውደ ርዕይ ይከፈታል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

 በሰምና ወርቅ ሚዲያና ኢንተርቴይመንት በየዓመቱ የሚዘጋጀውና አምስተኛ ዙር የሆነው “የአዲስ አመት ተስፋዎቻችን ለሀገራችን” የመፅሐፍት አውደ ርዕይ ረቡዕ  ነሀሴ 19 ቀን 2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ይከፈታል።  
እስከ ጳጉሜ 3 ለ14 ቀናት በሚቆየው በዚህ አውደ ርዕይ  በርካታ የመፅሐፍት መደብሮች የሚሳተፉ ሲሆን፣ ከገበያ  የጠፉና ተፈላጊ መፃህፍት ለሽያጭ እንደሚቀርቡና በሁሉም መፅሐፍት ላይ ከ20-50 በመቶ ቅናሽ እንደሚደረግባቸው የአውደርዕዩ አዘጋጅና የሰምና ወርቅ ሚዲያና ኢንተርቴይመንት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ዓለሙ ገልጿል።
በአውደ ርዕዩ ከግለ ታሪክ፣ እስከ ረጅምና አጭር ልቦለዶች፣ የትምህርት አጋዥ መፅሐፍት፣ የስነ-ልቦናና በርካታ አይነት መፅሐፍት በቅናሽ ለሽያጭ የሚቀርቡ ሲሆን ሁሉም አውደ ርዕዩን እንዲጎበኝና የሚፈልገውን መፅሐፍት እንዲገዛ አዘጋጆቹ ጋብዘዋል።


Read 9826 times