Saturday, 04 September 2021 17:44

ከፌስቡክ ገጾች በጨረፍታ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

“የትግራይ መከላከያ ኃይል ብሎ ነገር የለም!”
                                 ጌታሁን ሔራሞ


                  Jon Abbink ኔዜርላንዳዊ የአንትሮፖሎጂ እና የታሪክ ፕሮፈሰር ነው። በኢትዮጵያ የብሔር ፖለቲካና ብሔር-ተኮር ግጭቶች ላይ ጥናት ማድረግ ከጀመረ ዓመታት አልፈዋል። ጥናቶቹን ጎግል አድርጎ ማውረድና ማንበብ ይችላል። አንዱም ጥናቱ እ.ኤ.አ. በ2006 ይፋ የተደረገው “Ethnicity and Conflict Generation in Ethiopia: Some Problems and Prospects of Ethno-Regional Federalism” የተሰኘው ጥናቱ ነው። ፕሮፈሰሩ ከብሔር ፖለቲካ ጋር ጠበኛ ነው።
የዚህ ጽሁፍ ዓላማ ስለ ቀደምት የዮን አቢኒክ ጥናቶች ማውሳት አይደለም። ይልቁን ፕሮፈሰሩ ከአንድ ቀን በፊት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ጦርነት ዙሪያ አንድ ፅሁፍ ለቋል። ይህ ሰው ስለ ኢትዮጵያ የሚፅፈው ከውስጥ ሆኖ ነው፣ ስለዚህም እንደ አንዳንድ አውሮፓውያንና አሜሪካውያን እሱን መሸወድ የሚቻል አይደለም። ለምሣሌ ከአንድ ቀን በፊት ፕሮፈሰሩ ገና ከመግቢያው የፃፈው ፅሁፍ በግርድፉ ሲተረጎም ይህን ይመስላል፦
“የትግራይ መከላከያ የሚባል ነገር የለም፣ አሁን ራሳቸውን እንደዚያ ጠርተው ይሆናል፣ያለው ግን የትህነግ ሚሊሻ ነው፦ የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጪ ግንባር። ነፃ የወጣ የትግራይ መንግስት የሚባል ነገርም የለም፣ ስለዚህም የትግራይ መከላከያ ኃይል ብሎ ነገር የለም፤ በሕግ አግባብ የተፈጠረ እንደዚያ ዓይነት ሕጋዊ አካል የለም። እ.ኤ.አ ከ2018 በፊት በኢሕአዴግ ፓርቲ ውስጥ የአንበሳ ድርሻ የነበረው ትህነግ በኢትዮጵያ ላይ ሊነገሩ ዘንድ የሚያዳግቱ አደጋዎችን ፈፅሟል፣ ባለፉት ከ2-5 ዓመታት ደግሞ በራሱ የትግራይ ክልል ላይ አደጋን አድርሷል። ትህነግ እ.ኤ.አ.ከ1991-2018 ባለው ጊዜ የዘረጋው የብሔር ፖለቲካ በአፍሪካ ፀጉረ-ልውጡና የኢትዮጵያን ብሔሮች እርስ በእርሳቸው ያቃቀረ ፖለቲካ ነው።”
“There is no ‘TDF’: they may now call themselves like that but there is only the militia of the TPLF, the Tigray Peoples Liberation Front. There is no independent Tigrai state and hence no ‘TDF’: no entity like this was ever formed in a legal manner. TPLF (the former ruling regime in Ethiopia before February 2018, dominating the EPRDF party), has done untold damage to Ethiopia and in the past 2,5 years to Tigrai, ‘their own’ region. In 1991–2018 it installed a vicious politics of ethnicity ‘unique’ in Africa that has posited all so-called ethnic groups against each other, across the country.”
በነገራችን ላይ በየትኛውም የፌዴራል ሥርዓትን በሚከተሉ ሀገራት ክልሎች የራሳቸው መከላከያ ኃይል ብሎ ነገር የላቸውም። የመከላከያ ኃይል የሚኖራቸው በኮንፌዴሬሽን የተዋቀሩ አሊያም ሉዓላዊ ሀገራት ብቻ ናቸው። ፕሮፈሰር አቢኒክ ለዚህም ነው በተደጋጋሚ “የትግራይ መከላከያ ኃይል ብሎ ነገር የለም” የሚለው!
መልዕክት ለኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ፦
እባካችሁ በዚህ ፕሮፈሰር ፅሁፍ ዙሪያ በዓለም አቀፍ ቋንቋዎች ጭምር ሰፋ ያለ የዳሰሳ ሥራ ይሰራ።
ሰውዬው ለረዥም ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ በአካል ተገኝቶ ሕወሓት በነደፈው የብሔር ፖለቲካና ተያያዥ ግጭቶች ዙሪያ ጥናት ሲያደርግ ስለነበረ በዓለም አቀፍ ደረጃ ቅቡልነት ይኖረዋል። ኢሳት ቴሌቪዥን በአንድ ወቅት ቃለመጠይቅ እንዳደረገለት አስታውሳለሁ።


Read 1791 times