የአለማችን ቢሊየነሮች ቁጥር ባለፈው አመት ታይቶ በማይታወቅ መጠን በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመር 3ሺህ 204 መድረሱንና የቢሊየነሮቹ አጠቃላይ ሃብት 10 ትሪሊዮን ዶላር መድረሱን ዌልዝኤክስ የተባለው ተቋም ከሰሞኑ ባወጣው የ2021 አለማቀፍ የቢሊየነሮች ሁኔታ አመላካች ሪፖርት አስታውቋል፡፡
የቢሊየነሮች ቁጥር አምና ከነበረበት የ13.4 በመቶ ጭማሬ ማሳየቱን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ አጠቃላይ የሃብት መጠናቸው በአንጻሩ በ5.7 በመቶ ማደጉን አመልክቷል፡፡
ከአጠቃላዩ የአለማችን ቢሊየነሮች መካከል 60 በመቶ ያህሉ በራሳቸው ጥረት ለባለጸጋነት የበቁ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ከአለማችን አገራት መካከል በቢሊየነሮች ቁጥር ከፍተኛውን ጭማሪ ያስመዘገበቺው አሜሪካ መሆኗን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ በዓለም ላይ ከሚገኙት ቢሊየነሮች 29 በመቶ የሚሆኑት በአሜሪካ እንደሚገኙና ቻይና በ13 በመቶ፣ ጀርመን ደግሞ በ5 በመቶ እንደሚከተሉም አክሎ ገልጧል፡፡
በሌላ ኢኮኖሚ ነክ ዜና ደግሞ፣ አለማቀፉ ብድር በፍጥነት በማደግ ወደ 300 ትሪሊዮን ዶላር መድረሱን ኢንስቲቲዩት ኦፍ ኢንተርናሽናል ፋይናንስ የተባለው ተቋም ከሰሞኑ ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል፡፡ አለማቀፍ ብድሩ የመንግስታት፣ የግለሰቦች፣ የኩባንያዎችና የባንኮች ብድሮችን እንደሚያጠቃልል ተጠቁሟል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል