Print this page
Saturday, 25 September 2021 00:00

ሶስት ወንድማማች ደራሲያን አራት መፅሐፍት ዛሬ ይመረቃሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የሶስቱ  ወንድማማች ደራያን አራት መፅሐፍት ዛሬ በብሔራዊ ቴአትር ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ ይመረቃሉ፡፡ ደራሲያኑ ወንድማማቾች እንድሪያስ ይዘንጋው፣ ዳዊት ይዘንጋውና ወሰንሰገድ ይዘንጋው የሚባሉ ሲሆን ከአራቱ ሁለቱ ማለትም “ይሁዳ መዳፎች” እና “ዕድወት” የተሰኙ ልቦለድ መፅሀፎች የደራሲ እንድሪያስ ይዘንጋው፣ “የተረሳች” እና ሌሎች የደራሲ ዳዊት ይዘንጋው (ዳይተም) እንዲሁም “የፍሬሹ ሰበዞች” ደግሞ የደራሲ ወሰን ሰገድ ይዘንጋው ስራዎች መሆናቸው ታውቋል፡፡
ወንድማማቾቹ ደራሲያን፣ ዛሬ ረፋድ ላይ በብሔራዊ ቴአትር በሚያስመርቋቸው መፅሐፎች ሥነ- ሥርዓት ላይ አንጋፋ ደራሲያን የሚታደሙ ሲሆን የመፅሐፍቱ ዳሰሳ፣የግጥም ሥራዎች ሙዚቃና ሌሎች ኪነ-ጥበባዊ መሰናዶዎች ለታዳሚያኑ እንደሚቀርቡ ለማወቅ የተቻለ ሲሆን ወደ ምረቃ ሥነ ሥርዓቱ የሚመጡ ታዳሚያን የኮቪድ ፕሮቶኮል ታሳቢ እንዲያደርጉ ደራሲያኑ አሳስበዋል፡፡


Read 24117 times
Administrator

Latest from Administrator