Saturday, 25 September 2021 00:00

ኤገል ኮሌጅ በመጀመሪያ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በ2011 ዓ.ም ከከፍተኛ ትምህርት ጥራትና አግባብነት ኤጀንሲ በመጀመሪያ ዲግሪ እውቅና ባገኘባቸው በአካውንቲንግ ኤንድ ፋይናንስ እንዲሁም በማኔጅመንት የትምህርት አይነቶች በርቀት መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ባለፈው ቅዳሜ መስከረም 8 ቀን 2014 ዓ.ም ቃሊቲ በሚገኘው ካፍደም ሲኒማ አዳራሽ አስመረቀ፡፡
ኮሌጁ በ2011 በአዲስ አበባ ካምፓስ በነቀምቴ ጎንድር ግልገል በለስ ሰልጣኞችን በመመዝገብ ሲያስተምር የቆየ ሲሆን ለምርቃት ብቁ የሆኑ 186 ተማሪዎቹን ማስመረቁን የኮሌጁ ስራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ አቲቃ ገልፀዋል፡፡ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ  የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ሀላፊዎች፣ የኮሌጁ መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞችና እንዲሁም ተመራቂዎችና ቤተሰቦቻቸው ተገኝተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ስራውን እየሰራ ጎን ለጎን ያለውን የመማርና የራስን ማሻሻል ፍላጎት አጥንተው ይህን ፍላጎት ለመሙላት ኮሌጅን መክፈታቸውን የገለፁት አቶ ክፍሌ፤ ከኮሌጁም በተለያዩ የሀገሪቱ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የማስተማር ልምድ ባካበቱ ምሁራን መቋቋሙንና ዘንድሮ የመጀመሪያዎቹን ተመራቂዎች ማስመረቃቸውን አቶ ክፍሌ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም ኮሌጁ አቅሙን እያሳደገ፣ተጨማሪ የትምህርት አይነቶችንን እያስፋፋና ከስራው ጎን ለጎን መማር የሚፈልገውን የማህበረሰብ ክፍል በስፋት የማገልገል እቅድ እንዳለው የኮሌጁ ስራ አስኪያጅ ጨምረው ገልፀዋል፡፡

Read 23960 times