Wednesday, 29 September 2021 00:00

በድሃ አገራት 67 በመቶ ህጻናት በቂ ምግብ እንደማያገኙ ተነገረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ባለፉት አስር አመታት የህጻናትን የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ለመቀነስ የተደረጉ ጥረቶች ምንም አይነት ውጤት አለማስገኘታቸውን የገለጸው ተመድ፤ በማደግ ላይ በሚገኙ የአለማችን ድሃ አገራት ከሚኖሩ ህጻናት መካከል 67 በመቶ ያህሉ ለጤናማ የአካልና አእምሮ እድገት የሚያስፈልጋቸውን በቂ ምግብ እንደማያገኙ አስታውቋል፡፡
በተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ ባለፈው ረቡዕ ይፋ ባደረገው አዲስ ሪፖርት እንዳለው፣ በበርካታ የአለማችን ድሃ አገራት ከ6 ወር እስከ 23 ወር ዕድሜ ክልል ውስጥ ከሚገኙ ህጻናት መካከል ግማሽ ያህሉ በየዕለቱ ማግኘት የሚገባቸውን ዝቅተኛ የምግብ መጠን እያገኙ አይደለም፡፡  
የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝና የአየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ የተለያዩ ችግሮች በ91 የአለማችን አገራት ህጻናት የተመጣጠነ በቂ ምግብ እንዳያገኙና ለመቀንጨር እንዲዳረጉ ሰበብ መሆናቸውን የጠቆመው ሪፖርቱ፤ ህጻናት በተመጣጠነ ምግብ እጥረት ሳቢያ ትምህርታቸውን ለማቋረጥ እንዲሁም  በቀላሉ ለበሽታ እየተጋለጡና ለመቀንጨር እየተዳረጉ እንደሚገኙም አስታውቋል፡፡

Read 7749 times