Tuesday, 05 October 2021 00:00

ሰሜን ኮሪያ በአለማችን 3ኛውን እጅግ ግዙፍ ሚሳኤል ማስወንጨፏ ተነገረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የሰሜን ኮሪያ መንግስት ሁዋሶንግ 8 የተባለ እና በአለማችን በግዝፈቱ ሶስተኛ ደረጃን እንደሚይዝ የተነገረለትን እጅግ ፈጣን ሚሳኤል በተሳካ ሁኔታ ማስወንጨፉን ባለፈው ረቡዕ በይፋ አስታውቋል፡፡
የአገሪቱ መንግስት ማክሰኞ ዕለት እጅግ ፈጣን እንደሆነ የተነገረለትን ሃይፐር ሶኒክ ሚሳኤል ሙከራ በተሳካ ሁኔታ ማድረጉን መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡ ያስነበበው ቢቢሲ፤ የጦር መሳሪያው የአገሪቱን የመከላከያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ያሳድገዋል መባሉንም ገልጧል፡፡
ሰሜን ኮርያ ባለፈው አንድ ወር ጊዜ ውስጥ የሚሳኤል ሙከራ ስታደርግ ይህ ለሶሰተኛ ጊዜ መሆኑን ያስታወሰው ዘገባው፤ ከዚህ በፊት አዳዲስ ክሩዝ እና ከባቡር ላይ የሚወነጨፉ ባለስቲክ ሚሳኤሎችን መሞከሯንም አስረድቷል፡፡
ባለፈው ሳምንት በኒውዮርክ በተካሄደው የተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ አገራቸውን ወክለው በመገኘት ንግግር  ያደረጉት ኪም ሶንግ፤ ሰሜን ኮርያ ራሷን ለመከላከልና የሰላምና ደህንነት ሁኔታዋን አስተማማኝ ለማድረግ  ብሔራዊ መከላከያ እየገነባች እንደምትገኝ ማስታወቃቸው ይታወሳል፡፡

Read 1045 times