Tuesday, 19 October 2021 18:31

ሕጻናት ለእግዚአብሄር የጻፉት ደብዳቤ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ውድ እግዚአብሄር፡- እንዴት እስካሁን አዲስ እንስሳትን አልፈጠርክም? ከኛ ጋር ያሉት የድሮዎቹ ብቻ ናቸውን።
  ጆኒ
ውድ እግዚአብሄር፡- እግዚአብሄር መሆንህን እንዴት ነው ያወቅኸው?
  ሳሚ
ውድ እግዚአብሄር፡- ወንድ አያቴ ትንሽ ልጅ እያለም፣ አንተ ነበርክ፡፡ ዕድሜህ ግን ስንት ነው?
  ዴቭ
ውድ እግዚአብሄር፡- ማንም ከአንተ የተሻለ እግዚአብሄር ይሆናል ብዬ አላስብም። ይህን እንድታውቅልኝ እፈልጋለሁ። እንደዚህ የምለው ደሞ እግዚአብሄር ስለሆንክ ብቻ አይደለም፡፡
  ቻርልስ
ውድ እግዚአብሄር፡- እውነት በአይን አትታይም ወይስ ስትደን ነው?
  ሉሲ
ውድ እግዚአብሄር፡- ስቴፕለር ከታላላቆቹ ፈጠራዎችህ አንዱ ይመስለኛል።
  ሩት ኤም
ውድ እግዚአብሄር፡- ለአንተ ከሚሰሩልህ ሰዎች ሁሉ ጴጥሮስና ዮሐንስን በጣም እወዳቸዋለው።
  ሮዝ
ውድ እግዚአብሄር፡- አንዳንድ ነገሮች ከመፈጠራቸው በፊት ታውቃለህ እንዴ?
  ቻርልስ


Read 1112 times Last modified on Tuesday, 19 October 2021 18:41