የተለያዩ የአለማችን አገራትን የህግና ስርዓት ሁኔታ በመገምገም በየአመቱ ይፋ የሚያደርገው ጋሉፕ የተባለው ተቋም ከሰሞኑም የ2021 ሪፖርቱን ያወጣ ሲሆን፣ ኖርዌይ እንዳምናው ሁሉ ዘንድሮም በአንደኛ ደረጃ ላይ ስትቀመጥ ናሚቢያ፣ ማሊ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎና ዛምቢያ እጅግ የከፋ ሁኔታ ያለባቸው የአለማችን አገራት ናቸው ተብሏል፡፡
ተቋሙ ለበርካታ ሰዎች ቃለመጠይቅ በማድረግ በአገራት ውስጥ ያለውን የህግና ስርዓት ሁኔታ ለመገምገም ከሚጠቀምባቸው መስፈርቶች ውስጥ ዜጎች ምን ያህል በፖሊስ ላይ እምነት አላቸው፣ ደህንነት ይሰማቸዋል፣ ዝርፊያና ሌሎች ጥቃቶች ደርሶባቸዋል የሚሉት እንደሚገኙበት የተነገረ ሲሆን፣ የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች፣ ቻይናና ስዊዘርላንድ በተመሳሳይ ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዘዋል፡፡
በአመቱ በተመሳሳይ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን የያዙት የአለማችን አገራት ደግሞ ፊንላንድ፣ አይስላንድና ታጃኪስታን መሆናቸውን የተቋሙ ሪፖርት ያሳያል፡፡ ደቡብ አፍሪካ በከፋ የህግና ስርዓት ሁኔታ የሁለተኛነት ደረጃን የያዘች ሲሆን፣ ናይጀሪያና ፔሩ በተመሳሳይ ነጥብ የሶስተኛ ደረጃን መያዛቸውንም መረጃው ያመለክታል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል