Thursday, 25 November 2021 00:00

ኖርዌይ ህግና ስርዓት የሰፈነባት ቀዳሚዋ አገር ናት ተባለ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

   የተለያዩ የአለማችን አገራትን የህግና ስርዓት ሁኔታ በመገምገም በየአመቱ ይፋ የሚያደርገው ጋሉፕ የተባለው ተቋም ከሰሞኑም የ2021 ሪፖርቱን ያወጣ ሲሆን፣ ኖርዌይ እንዳምናው ሁሉ ዘንድሮም በአንደኛ ደረጃ ላይ ስትቀመጥ ናሚቢያ፣ ማሊ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎና ዛምቢያ እጅግ የከፋ ሁኔታ ያለባቸው የአለማችን አገራት ናቸው ተብሏል፡፡
ተቋሙ ለበርካታ ሰዎች ቃለመጠይቅ በማድረግ በአገራት ውስጥ ያለውን የህግና ስርዓት ሁኔታ ለመገምገም ከሚጠቀምባቸው መስፈርቶች ውስጥ ዜጎች ምን ያህል በፖሊስ ላይ እምነት አላቸው፣ ደህንነት ይሰማቸዋል፣ ዝርፊያና ሌሎች ጥቃቶች ደርሶባቸዋል የሚሉት እንደሚገኙበት የተነገረ ሲሆን፣ የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች፣ ቻይናና ስዊዘርላንድ በተመሳሳይ ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዘዋል፡፡
በአመቱ በተመሳሳይ ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን የያዙት የአለማችን አገራት ደግሞ ፊንላንድ፣ አይስላንድና ታጃኪስታን መሆናቸውን የተቋሙ ሪፖርት ያሳያል፡፡ ደቡብ አፍሪካ በከፋ የህግና ስርዓት ሁኔታ የሁለተኛነት ደረጃን የያዘች ሲሆን፣ ናይጀሪያና ፔሩ በተመሳሳይ ነጥብ የሶስተኛ ደረጃን መያዛቸውንም መረጃው ያመለክታል፡፡

Read 5209 times