የደራሲ አማረ ተግባሩ (ዶ/ር) “ፀሐዩ ዕንቁ ስላሴ ፀረ ፋሽሽት እርበኛና የሀገር ባለውለታ” መፅሐፍ ዛሬ ህዳር 18 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ይመረቃል፡፡ በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጅግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ተገኝተው ንግግር የሚያደርጉ ሲሆን ደጃዝማች ወልደ ሰማያት ወልደ ገብርዔል በክብር እንግድነት እንደሚገኙና ትውስታቸውን እንደሚያካፍሉም ታውቋል፡፡ ደራሲ እንዳለ ጌታ ከበደ(ዶ/ር) በመፅሐፉ ላይ ደሰሳ የሚያቀርብ ሲሆን፣ደራሲ ይታገሱ ጌትነት ግጥም፣ ፀሐፊ ተውኔት ገጣሚና ደራሲ አያልነህ ሙላትና ከያኒ ጌትነት እንየው በባለታሪኩ አርበኛ ዙሪያ ምስክርነት እንደሚያቀርቡም ታውቋል፡፡ ጋዜጠኛ ሚካኤል አለማየሁ (የዕናኑ ልጅ) መድረኩን የሚያጋፍር ሲሆን፣ ደራሲው አማረ ተግባሩ (ዶ/ር) በመፅሀፋቸው ዙሪያ ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ለማወቅ ተችሏል፡፡
“ፀሀዩ እንቁስላሴ ፀረ ፋሽስት አርበኛና የሀገር ባለውለታ” መፅሐፍ ዛሬ ይመረቃል
Written by AdministratorLatest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል