Saturday, 15 January 2022 17:02

የመከላከያ ጀግኖች የተወደሱበትና የተዘከሩበት መርሃ ግብር

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  "ክብር ለመከላከያ ሰራዊታችን" የተሰኘው ኢምር በኮልፌ 2014 ቶርናመንት፣ ባለፈው እሁድ፣ በኮልፌ መላጣ ሜዳ፣ በተለያዩ የስፖርትና የኪነ ጥበብ ዝግጅቶች በከፍተኛ ድምቀት መካሄዱ ታውቋል፡፡
"በመክፈቻ ፕሮግራሙ ላይ ጀግኖች ተመስግነዋል፣ ለሀገራቸው ከፊት የቀደሙ ተወድሰዋል፣ ኢትዮጵያን ዘብ ሆነው ሁሌም የሚያገለግሉ ተዘክረዋል፡፡" ብለዋል፤ የቶርናመንቱ አዘጋጆች፡፡
ከዚህ በተጨማሪም የደም ልገሳ የተደረገ ሲሆን በስፖርት ጋዜጠኞችና በኮሜዲያን መካከል የእግር ኳስ ጨዋታ መካሄዱ ታውቋል፡፡ የቦክስ ግጥሚያና አስደናቂ የሰርከስ ትርኢቶችም የፕሮግራሙ ድምቀቶች ነበሩ ተብሏል፡፡ በእሁዱ የመክፈቻ ፕሮግራሙ ላይ የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማ ስራ አስፈፃሚዎች፣ አርቲስቶች፣ የቀድሞ የእግር ኳስ ዝነኛ ተጫዋቾች እንዲሁም የኮልፌ ነዋሪዎች ተገኝተው ነበር።

Read 8429 times