በፊልም ገቢና በሲኒማ ቤቶች ብዛት ከአለም 1ኛ ደረጃን ይዛለች በአገሪቱ 82,248 ሲኒማ ቤቶች ይገኛሉ
የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የአለማችንን የፊልም ኢንዱስትሪ ክፉኛ በጎዳበት ያለፈው የፈረንጆች አመት 2021 በአገረ ቻይና 6 ሺህ 667 አዳዲስ ሲኒማ ቤቶች ተገንብተው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውና አገሪቱ በአመቱ ከቦክስ ኦፊስ 7.4 ቢሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት ከአለም አገራት 1ኛ ደረጃን መያዟ ተነግሯል፡፡
ቻይና በ2021 የፈረንጆች አመት ከቦክስ ኦፊስ ካገኘችው አጠቃላይ ገቢ 85 በመቶ ያህሉን ያገኘችው በአገር ውስጥ ከሰራቻቸው ፊልሞች መሆኑን የዘገበው ግሎባል ታይምስ፣ በአመቱ 6 ሺህ 667 አዳዲስ ሲኒማ ቤቶችን መክፈቷንና የሲኒማ ቤቶቿን አጠቃላይ ቁጥር ወደ 82,248 ከፍ በማድረግ ባለብዙ ሲኒማ ቤት አገር ለመሆን መብቃቷንም አመልክቷል፡፡