Print this page
Monday, 14 March 2022 00:00

“ፍህት ይንገስ ሰላም ይመለስ” የኪነ ጥበብ ዝግጅት ሰኞ ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዩሴፍ
Rate this item
(0 votes)

  በምስክር ጌታነው ሚዲያና ፕሮሞሽን የተዘጋጀውና  “ፍትህ ይንገስ ሰላም ይመለስ” የሚል መጠሪያ ያለው የኪነ-ጥበብ መሰናዶ ሰኞ መጋቢት 5 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር ይካሄዳል፡፡
በዕለቱም ዲስኩር፣ ግጥም ፣መነባነብና ሙዚቃ የሚቀርብ ሲሆን ጋዜጠኛ እስክንድ ነጋ፣መምህር ፋንታሁን ዋቄ፣ ዶ/ር ወዳጄነህ መሃረነ፣ የህግ ባለሙያ ውብሸት ሙላት ዲስኩር፣ ገጣሚያኑ ዲያቆን መኩሪያ ጉግሳ፣ ሻለቃ የወይንሃረግ በቀለ፣ ገዛኸኝ ፀጋው (ዶ/ር)፣ ዘቢብ መልኬ ግጥም እንዲሁም ህጻን አሜን ካሳሁን መነባነብ እንደሚያቀርቡም ታውቋል፡፡
ሻሎም ለኢትዮጵያ የሙዚቃ ቡድን ከድምፃዊያን ጋር በሙዚቃ በሚያደምቀው በዚህ ልዩ የኪነ-ጥበብ ድግስ ለመታደም የመግቢያ ዋጋ 100 ብር እንደሆነና የመግቢያ ትኬቶቹም በጃፋር፣ አይናለምና ዮናስ መፃሀፍት መደብሮች እንዲሁም በጣይቱ ሆቴልና ካሳንቺስ በሚገኘው ጆሲ ልብስ ስፌት ቤት ይገኛሉም ተብሏል፡፡

Read 9050 times