እስከ ጊዜው ድረስ
እስከ ጊዜው ድረስ
በተያዘው ሳቁ - ከማይቀረው ራቁ
ወረፋ ነውና ተራችሁን ጠብቁ
ይመስላል የማይፈርስ
ጥበቃም የማይደርስ
ሀዘንም የማይመር
ምኞትም የማይሰምር
የረገበ ሁሉ - ዝንታለም የማይከር
የማይመስል ይመስላል!
ግን፤ ድንጋይም በሂደት
እንደ ወይን ይበስላል
ፀሀይዋም አንድ ቀን
ቀይ ድዷ ይከስላል
ጊዜ አረፋ ነው
ባላ’ረፋ ወንዝ ነው
የማይደርስ ይመስላል
ስቆ ያሳስቃል
ተራ ያስጠብቃል፡፡
(ሌሊሣ ግርማ)