Saturday, 23 April 2022 15:03

ባይደን "ትራምፕን የማሸንፈው እኔ ብቻ ነኝ፤ በድጋሚ እወዳደራለሁ" አሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

     የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በቀጣዩ የ2024 ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በድጋሚ እንደሚወዳደሩና ዶናልድ ትራምፕን ተፎካክሮ ማሸነፍ የሚችለው ብቸኛው ሰው እኔ ነኝ ብለው እንደሚያስቡ መናገራቸው ተዘግቧል፡፡
ባይደን ይህንን የተናገሩት ለቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ መሆኑን ሰሞኑን ባወጣው ዘገባ ያስነበበው ዘ ሂል ድረገጽ፣ በ78 አመታቸው ምርጫ አሸንፈው ወደ ነጩ ቤተመንግስት የገቡትና በእድሜ አንጋፋው ስልጣን የያዙ ቀዳሚው የአሜሪካ መሪ የሆኑት ባይደን፣ እንዳሉት በቀጣዩ ምርጫ የሚወዳደሩና የሚያሸንፉ ከሆነ፣ ሁለተኛ ዙር የስልጣን ዘመናቸውን የሚጀምሩት በ82 አመታቸው እንደሚሆንም ጠቁሟል፡፡
የ75 አመቱ ትራምፕ በበኩላቸው፤ በቅርቡ በቀጣዩ ምርጫ እንደሚወዳደሩና ባይደንን በሰፊ ልዩነት እንደሚያሸንፉ በይፋ መናገራቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ በቅርቡ የተሰሩ ጥናቶች ከባይደን ይልቅ ትራምፕ የበለጠ የማሸነፍ ዕድል እንዳላቸው የሚያመለክቱ መሆናቸውንም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1845 times