በ7 ቀናት የሞቱት 15 ሺህ ያህል ሰዎች ብቻ ናቸው
እስካለፈው ረቡዕ የነበረው አንድ ሳምንት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ተስፋፍቶ ከጀመረበት መጋቢት ወር 2020 ወዲህ በመላው አለም ዝቅተኛው የኮሮና ሟቾች ቁጥር የተመዘገበበት እንደሆነና በሰባት ቀናት ውስጥ በቫይረሱ ለሞት የተዳረጉት ሰዎች ቁጥር 15 ሺህ ያህል ብቻ መሆኑን የአለም የጤና ድርጅት አስታውቋል፡፡
የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ፣ የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር ቅናሽ ማሳየት መጀመሩ ተስፋ ሰጪ ቢሆንም፤ የምርመራ መጠን መቀነሱ ቫይረሱን በቁጥጥር ስር ለማዋል የሚደረገውን ጥረት ሊያሰናክል የሚችል ነው ሲሉ ማስጠንቀቃቸውንም አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
ቫይረሱ ለሞት የዳረጋቸው ሰዎች ቁጥር 6 ሚሊዮን ያህል ነው ተብሎ በይፋ ቢነገርም፣ ትክክለኛው መጠን ግን ከሚባለው ከሶስት እጥፍ በላይ ሊበልጥና 18 ሚሊዮን ሊደርስ እንደሚችል በቅርቡ በላሰንት መጽሄት ላይ የወጣ ጥናት ማመልከቱንም ዘገባው አስታውሷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል