በአልበሙ ላይ በግጥምና ዜማ ከተሳተፉት መካከል ነዋይ ደበበ፣ አንተነህ ወራሽና አለማየሁ ደመቀ ሲገኙበት በሙዚቃ ቅንብር ካሙዙ ካሣ፣ ሚካኤል ሃይሉና መኮንን ለማ (ዶክተሬ) ሰርተዋል፡፡ “የፍቅር ጥሪ” የሚለውን ስያሜ ሁለት ዘፈኖች የሚወክል እንደሆነ ስንታየው ገልፆ፤ አንደኛው ዘፈን የፍቅር አጋሩን ስለሚፈልግ ወጣት የተጫወትኩበት ነው ብሏል፡፡ “መነድ አያዶ” የሚለው ዘፈን ደግሞ በሃድያ ባህል ሰዎች ለፍቅር የሚገናኙበትን መንገድ የሚገልጽ ሲሆን፣ 83 የአገራችን ብሔረሰቦች እርስበርስ እንዲገናኙበት ጥሪ በማድረግ የሠራሁበት ነው ብሏል፡፡