Print this page
Monday, 16 May 2022 20:07

የቀድሞው የናይጀሪያ መሪ በድጋሚ እንዲወዳደሩ የቀረበላቸውን ጥሪ አልተቀበሉም

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የቀድሞው የናይጀሪያ ፕሬዚዳንት ጉድላክ ጆናታን በቅርቡ በሚካሄደው የአገሪቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በድጋሚ እንዲወዳደሩ ከአንድ የአገሪቱ ፓርቲ ደጋፊዎች ጥሪ ቢቀርብላቸውም ሳይቀበሉት መቅረታቸውን ኦል አፍሪካን ኒውስ ዘግቧል፡
የአገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን ፓርቲዎች ለቀጣዩ ምርጫ የሚያቀርቡትን ዕጩ እስከ ሰኔ 3 እንዲያሳውቁ ቀነ ገደብ ማስቀመጡን ያስታወሰው ዘገባው፤ ኦል ፕሮግረሲቭ ኮንግረስ የተባለውና ጉድላክ ጆናታን በ2015 ለድጋሚ የስልጣን ዘመን ባደረጉት ውድድር ያሸነፋቸውና በስልጣን ላይ ያለው ፓርቲ ደጋፊዎች የሆኑ ግለሰቦች ጆናታን ፓርቲውን ወክለው በድጋሚ እንዲወዳደሩ የምርጫ መወዳደሪያ ምዝገባ ሰነዱን ከሚመለከተው አካል ገዝቶ ቢወስድላቸውም እሳቸው ግን፣ "ትልቅ ንቀት ነው" በማለት ጥሪውን አጣጥለውታል፡፡
ጉድላክ ጆናታን እ.ኤ.አ በ2010 በተካሄደ ምርጫ አሸንፈው አገሪቱን ለ5 አመታት በፕሬዚዳንትነት ማስተዳደራቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ በምርጫ አሸንፎ ስልጣን የተረከባቸውን ፓርቲ ወክለው እንዲወዳደሩ ደጋፊዎቻቸው ሰነዱን በ240 ሺህ ዶላር ያህል ገዝተው ቢያመጡላቸውም ፈቃደኛ ሳይሆኑ መቅረታቸውን አመልክቷል፡፡

Read 1298 times
Administrator

Latest from Administrator