Wednesday, 18 May 2022 00:00

40 በመቶ የአለም ህዝብ የውሃ እጥረት ሰለባ ነው ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ከአጠቃላዩ የአለማችን ህዝብ 40 በመቶ ያህሉ የከፋ የውሃ እጥረት ችግር ሰለባ መሆኑንና በመላው አለም በመጪዎቹ ሰባት አመታት ጊዜ ውስጥ በድርቅ ሳቢያ 700 ሚሊዮን ያህል የተለያዩ አገራት ዜጎች ከመኖሪያ አካባቢያቸው ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ ተነገረ፡፡
የአለም የጤና ድርጅት በቅርቡ ያወጣው አንድ የጥናት ውጤት እንደሚለው፣ በየአመቱ በመላው አለም 55 ሚሊዮን ያህል ሰዎች በውሃ ወይም ዝናብ እጥረት ሳቢያ በሚከሰት ድርቅ ተጎጂ ይሆናሉ፡፡
የአለማችን ህዝብ ቁጥር በፍጥነት እያደገ ከመሄዱ ጋር ተያይዞ ውሃን የመሳሰሉ ውስን የተፈጥሮ ሃብቶች በከፍተኛ መጠን ጥቅም ላይ እየዋሉና ከፍተኛ እጥረት እየተከሰተ እንደሚገኝ የጠቆመው መረጃው፤ የአየር ንብረት ለውጥ በአለማችን የውሃ ሃብት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እየፈጠረ እንደሚገኝም አመልክቷል፡፡
በመጪዎቹ 35 አመታት ከ570 በላይ በሚሆኑ የአለማችን ከተሞች የሚኖሩ 685 ሚሊዮን ያህል ሰዎች የንጹህ ውሃ አቅርቦታቸው በ10 በመቶ ያህል ይቀንሳል ተብሎ እንደሚገመት የጠቆመው መረጃው፤ ይህም በበርካታ የአለማችን አገራት ጥቅል የአገር ውስጥ ምርት ላይ ከፍተኛ የሆነ አሉታዊ ተጽዕኖ ያደርሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ያብራራል፡፡

Read 5885 times