Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 13 October 2012 10:50

አዲሱ ጠ/ሚ በተገኙበት የመጀመርያው የፓርላማ ውይይት ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(14 votes)

የወ/ሮ አዜብ ቤት አለማስረከብ እያወዛገበ ነውከትናንት በስቲያ መደበኛ ስብሰባውን ለማካሄድ የተሰበሰበው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በገዢው ፓርቲ በኩል የቀረበውን ሞሽን ከማጽደቁ በፊት አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር በተገኙበት ውይይት እንዲደረግበት ከአፈ ጉባኤው አባዱላ ገመዳ ሐሳብ በመቅረቡ ለመጪው ማክሰኞ እንዲያድር ተወሰነ፡፡ ጠ/ሚሩ በመጪው ማክሰኞ ፓርላማ ተገኝተው የመጀመሪያ ውይይት ያደርጋሉ ተብሏል፡፡ መስከረም 28 ቀን 2005 ዓ.ም ፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ በፓርላማ ተገኝተው  የሕዝብ ተወካዮችና የፌደሬሽን ምክር ቤቶችን የጋራ መደበኛ ስብሰባ በንግግር ከከፈቱ በኋላ ጥቅምት 1 ቀን የመጀመሪያ መደበኛ ስብሰባውን ለማካሄድ የተበሰበበው ምክር ቤቱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሌሉበት ሞሽኑ መጽደቅ ስለሌለበት አጀንዳው እስከመጪው ማክሰኞ ይደር ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል በጠቅላይ ሚኒስትርነት ከተሾሙ ከ20 ቀናት በላይ ያስቆጠሩት አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ እስካሁን ቤተመንግስት አለመግባታቸው ተገቢ አይደለም ተባለ፡፡ የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን የጠ/ሚኒስትር መለስን የ80ኛ ቀን ተዝካር ሳያወጡ ቤተመንግስቱን ለመልቀቅ አለመፍቀዳቸውን የጠቀሱ ምንጮች ጉዳዩ ትክክል አይደለም ሲሉ ተችተዋል፡፡ አዲሱ ጠ/ሚኒስትር ብስራተ ገብርኤል አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው እየተመላለሱ አገሪቱን ማስተዳደራቸው ለአገሪቷም ክብር ጭምር ተገቢ እንዳልሆነ አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል፡፡ ወ/ሮ አዜብ ቤተመንግሥቱን ማስረከባቸው ላይቀር ውዝግብ ማስነሳቱ ተገቢ አይደለም የሚሉት አስተያየት ሰጪዎች፤ አገሪቱን የሚያስተዳድሩት አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር በውጭ ሆነው እሳቸው ከውስጥ መቀመጣቸው ሌላ ትርጉም ያሰጠዋል ብለዋል፡፡

 

Read 4310 times Last modified on Saturday, 13 October 2012 10:54