Saturday, 23 July 2022 15:05

ፀሐይ ባንክ ዛሬ በ30 ቅርንጫፎች ሥራ ይጀምራል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የአገሪቱን የንግድ ህግና የብሄራዊ ባንክ መመሪያ በማሟላት የተቋቋመው ጸሃይ ባንክ፣ ዛሬበይፋስራእንደሚጀምርአስታወቀ።
ባንኩ ይህን ያስታወቀው ከትላንትበስቲያ ረፋድ ላይ በሃያት ሬጀንሲ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው። እንደባንኩሃላፊዎች ገለፃ፤ "ፀሐይ ባንክ ለሁሉም "በሚልመሪቃል፣ ዛሬ ስራውን የሚጀምር ሲሆንበ2.9  ቢሊዮን ብርየ ተፈረመ፣ በ734 ሚሊዮን ብር ሥራ ላይ የዋለ ካፒታልና በ373 ባለአክሲዮኖች መዋቀሩንም የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶታዬ ዲበኩሉ፣ምክትል የቦርድ ሰብሳቢው አቶ ታደሰ አየነውና የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ያሬድ መስፍን

በጋራ በሰጡት መግለጫ አብራርተዋል።
   ፀሐይ ባንክ፣ የባንክ ኢንዱስትሪውን ክፍተት በተረዱና ለትውልድ የሚሸጋገር ተቋም ለመመስረት ዓላማ ባላቸው አደራጆች የተቋቋመ ሲሆን ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ሊያገለግል በሚያስችል አደረጃጀት ዝግጅቱን አጠናቅቆ ዛሬ በይፋ ስራ እንደሚጀምር ሃላፊዎቹ ጨምረው ገልፀዋል። የፀሐይ ባንክ ዓላማ የባንክ ኢንዱስትሪውን መቀላቀል ብቻ ሳይሆን በፋይናንስ ዘርፉ በቂ ትኩረት ያላገኙትን የጥቃቅንና አነስተኛ፣ የግብርናውን ዘርፍ ፣የአምራች የአምራች ኢንዱስትሪዎችንና አዋጭ የሆኑ የፈጠራ ሃሳቦችንና ስራ ፈጣሪዎችን ተደራሽ በማድረግ እንደ መሪ ቃሉ የሁሉም አገልጋይ እንዲሆን መትጋት ነው ብለዋል ሃላፊዎቹ። ባንኩ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን በማዘመን፣ ዘመኑን የዋጀ “ቴሚኖስ ትራንዛክትአር 21” የለቀቀውን የኮርባን ኪንግ ሲስተም በመላበስ፣ መደበኛውን የባንክ አገልግሎትና ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት እንዲሁም የቢፒሲ ኩባንያ ምርት “ስማርትቪስታ” በመጠቀም አጠቃላይ የዲጂታል ባንክ አገልግሎት ይዞ በመቅረብ በኢንዱስትሪው ውስጥ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑን የቦርድ ሰብሳቢው አቶ ታዬ ዲበኩሉ ተናግረዋል።
እንደ ሃላፊዎቹ ገለፃ፤ ዛሬ ባንኩ በይፋ አገልግሎቱን መስጠት ሲጀምር 30 ቅርንጫፎቹ በተመሳሳይ ሰዓት ሥራ የሚጀምሩ ሲሆን፣ በቅርቡም የቅርንጫፎቹን ብዛት ወደ 50 እንደሚያሳድግ ተብራርቷል። ባንኩ ዛሬ ስራውን በይፋ በሚያስጀምርበት ስነ ስርዓት ላይ የብሄራዊ ባንክ ከፍተኛ አመራሮች፣ የተለያዩ
ባንኮች የቦርድ አመራሮችና ፕሬዚደንቶች፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚታደሙም ታውቋል፡፡


Read 12511 times Last modified on Saturday, 23 July 2022 15:20