Saturday, 17 September 2022 12:51

የዱባይ ቱሪዝም የምስራቅ አፍሪካ ከተሞች ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ተካሄደ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የዱባይ ቱሪዝም የምስራቅ አፍሪካ ከተሞች ኤግዚቢሽን ባለፈው ረቡዕና ሐሙስ  ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል ተካሂዷል።  የኤግዚቢሽኑ ዓላማ  በኢትዮጵያ ካሉ የዘርፉ ባለድርሻ አካላት  ጋር በቅርበት በመስራት ዱባይ በውድ ዋጋ ብቻ ሳይሆን በተመጣጣኝ ክፍያ መጎብኘት የሚቻልባቸውን መንገዶች ማስተዋወቅ  ነው ተብሏል፡፡
የዱባይ ቱሪዝም የዓለም አቀፍ ግንኙነት ረዳት ሥራ አስፈጻሚ ሚስተር ታሪቅ ቢንብሬክ ኤግዚቢሽኑን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፤ “ምስራቅ አፍሪካ በተለይ በዱባይ ቱሪዝም ትልቅ ግምት የሚሰጠው ገበያ ሲሆን ከአፍሪካ ትልቁ የተጓዥ ቁጥር የሚመነጨው ከዚሁ ስፍራ ነው፤ ይህ ያሁኑ ኤግዚቢሽን ከኮቪድ ወረርሽኝ በኋላ የመጀመሪያው ነው፤ እኛም በመመለሳችን ደስተኞች ነን፤” ብለዋል፡፡በዚህ መርሃግብር  ከዱባይ ቱሪዝም ጋር ከ25 የማያንሱ ድርጅቶች ተወካዮቻቸውን ወደ አዲስ አበባ  የላኩ ሲሆን ከትናንት በስቲያ ሐሙስ  ሥራቸውን በማቅረብ፣ በኢትዮጵያ ከሚገኙ የአስጎብኚ ድርጅቶችና ባለድርሻ አካላት ጋር ትውውቅ አድርገዋል።ባለፈው ረቡዕ በተሰጠው ሥልጠና የተሳተፉት ከ100 በላይ የሆኑ የሀገራችን የቱር እና ትራቭል ተቋማት ሲሆን ስልጠናውን የሰጡት ደግሞ የዱባይ ቱሪዝም ኢንተርናሽናል ኦፕሬሽንስ ሰብሰሀራን አፍሪካ ዳይሬክተር ስቴላ ፉባራ እና ምክትላቸው ታሬክ ቢንብሬክ ናቸው።በመዝጊያ መርሀ ግብሩ ለተሳታፊዎች ዕጣ የማውጣት ስነ ስርዓት የተካሄደ ሲሆን፤ ዕድለኞቹ ወደ ዱባይ የሚጓዙ ይሆናል ተብሏል።
ከዚህ ቀደም ምንም የትውውቅ መድረክ ሳይኖር ኢትዮጵያ ከሰሀራ በታች ከሚገኙ የአፍሪካ ሀገራት ወደ ዱባይ በሚደረግ የንግድና የቱሪዝም ጉዞ ከናይጄሪያ ቀጥላ ሁለተኛ ሀገር መሆኗም ተጠቁሟል፡፡

Read 11403 times