Saturday, 08 October 2022 09:32

የአውሮፓ ህብረት ፓርላማ የሰሜኑ ግጭት በአስቸኳይ እንዲቆም ጠየቀ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

      ህፃናት ለጦርነት እየተመለመሉ መሆኑን አውግዟል

                        ህፃናት ለጦርነት እየተመለመሉ መሆኑን አውግዟል

       የአውሮፓ ህብረት ፓርላማ ከትላንት በስቲያ በኢትዮጵያ ጉዳይ ከተወያየ በኋላ ባወጣው የውሳኔ ሃሳብ፤ በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ግጭት በአስቸኳይ ቆሞ በትግራይና በአዋሳኝ ክልሎች ያለአንዳች ቅድመ ሁኔታ ተኩስ አቁም እንዲደረግ ጠይቋል።
በሰሜኑ ግጭት ህፃናት ለጦርነት ይመለመላሉ መባሉንና ነፍጥ አንግተው በጦር ግንባር እንዲሰለፉ መደረጉን  እንደሚያወግዝም ህብረቱ አስታውቋል።
“በጦርነት በተጎዱ አካባቢዎች ለሚገኙ ወገኖች በሙሉ የተሟላ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ዘላቂ የሰብአዊ እርዳታ እንዲደርሳቸው የአውሮፓ ህብረት ፓርላማ አባላት ይሻሉ” ብሏል፡፡
ህብረቱ  ባወጣው የውሳኔ ሃሳብ፡፡ የሰላማዊ ሰዎችን ሆነ ብሎ ዒላማ ማድረግና ህፃናትን ለውትድርና መመልመል በጦር ወንጀልና በሰብአዊነት ላይ የሚፈፀም  ወንጀል መሆኑን  ፓርላማው አውስቷል፡፡
የሰሜን ኢትዮጵያን ጦርነትን ተከትሎ በትግራይ ከሚገኙት ከ5 ዓመት በታች ከሆኑት ሶስት ህጻናት ውስጥ አንዱ የምግብ እጥረት እንደሚያጋጥመው የጠቆመው ፓርላማው፣ የትግራይ ነብሰ ጡር ከሆኑና ከሚያጠቡ እናቶች መካከል ደግሞ ገሚሱ የምግብ እጥረት ተጠቂ መሆናቸውን አመልክቷል፡፡
በክልሉ በጦርነቱ ሳቢያ ከትምህርት ገበታ የተለዩ ህፃናት ቁጥር 1.39 ሚሊዮን እንደሆነም ፓርላማው ጠቁሟል።
ህብረቱ ባወጣው የውሳኔ ሃሳብ፤ ተፋላሚ ሃይሎች ልዩነቶቻቸውን በውይይት እንዲፈቱ የጠየቀ ሲሆን በተለይም በአፍሪካ ህብረት መሪነት የሚደረገውን የሰላም ጥረት እንደሚደግፍ አስታውቋል፡፡
አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች፤ የአውሮፓ ህብረት ፓርላማ ህፃናት ለውትድርና መመልመላቸውን ማውገዙ ተገቢ ቢሆንም፤ በእጅጉ ግን ዘግይቷል ሲሉ ተችተዋል፡፡ አማፂው ህውሓት ቡድኑ ብዙ ሺህ ህፃናት ለጦርነቱ ተመልምለው ማለቃቸውን በመግለፅ፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት የዛሬ ዓመት ግድም ጀምሮ የአማፂው ቡድን ህፃናትን ነፍጥ አሲዞ ለጦርነት እያዘመተ መሆኑን በማጋለጥ ዓለማቀፉ ማህበረሰብ ድርጊቱን እንዲያወግዝ በተደጋጋሚ ቢወተውትም ዓለማቀፉ ማህበረሰብ ያልሰማ መስሎ አልፎታል ሲሉ ነቅፈዋል፡፡


Read 11719 times