Saturday, 08 April 2023 19:35

በአቶ ሽመልስ አብዲሳ ስም በተደራጀ ማህበር ሲሚንቶ ሲያከፋፍሉ ነበር የተባሉ ተከሳሾች ተቀጡ

Written by 
Rate this item
(7 votes)

በአቶ ሺመልስ አብዲሳ ስም በህገወጥ መንገድ በተደራጀ ማህበር ሲሚንቶ ሲያከፋፍሉ ነበር በተባለ ተከሳሾች ላይ የእስራትና የገንዘብ ቅጣት ውሳኔ ተሰጠ፡፡
የኦሮሚያ ክልል ሽገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወንጀል ችሎት ትናንት በዋለው ችሎት በሰጠው ውሳኔ ላይ እንደተገለፀው ተከሳሾች በኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሺመልስ አብዲሳ ስም ሀሰተኛ ሰነድ በመጠቀም በህገ-ወጥነት በተደራጀው ማህበር ከ29 ሚሊዮን ብር በላይ የሚወጣ ሲሚንቶ በማውጣት ለግል ጥቅማቸው አውለዋል። ፍርድ ቤቱ በተከሳሾች ላይ የቀረቡትን ማስረጃዎች ከመረመረ በኃላ በመዝገቡ ከተከሰሱ ተከሳሾች መካከል በስምንቱ ላይ እስከ 20 ዓመት በሚደርስ እስራትና በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወሰኗል፡፡የቅጣት ውሳኔው ከተላለፈባቸው ተከሳሾች መካከል የኦሮሚያ ክልል የደህንነት ባለሙያ አቶ አዲሱ አንጋሳ የሚገኙበት ሲሆን የቀድሞ የኦሮሚያ ክልል የንግድ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ወርቁ ጫላም ከተከሳሾቹ መካከል ይገኙበታል፡፡
ፍርድ ቤቱ የኦሮሚያ ክልል የደህንነት ባለሙያ በነበረው ተከሳሽ አቶ አዲሱ አንጋሳ ላይ የሃያ አመት ፅኑ እስራትና የሁለት መቶ ሺብር የገንዘብ ቅጣት የወሰነባቸው ሲሆን በክልሉ የቀድሞ የንግድ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ወርቁ ጫላ ላይ ደግሞ የአምስት አመት ፅኑ እስራትና 10ሺ ብር የገንዘብ ቅጣት ወስኗል፡፡
ፍርድ ቤቱ በተከሳሾች እጅ ላይ የተገኙ 8ሺ ኩንታል ሲሚንቶ እና ከ565 ሺ ብር በላይ ገንዘብ እንዲወረስ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

Read 2331 times