Saturday, 13 May 2023 20:01

50ኛው የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀን በተለያዩ መርሃ ግብሮች ሊከበር ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

50ኛው የአለም አካባቢ ጥበቃ ቀን ከግንቦት 25-27 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ጎልፍ ክለብ ጋርደን ውስጥ ይከበራል፡፡
“የፕላስቲክ ብክለትን እንግታ” በሚል መሪ ቃል ለ3 ቀናት በሚከበረው በዚሁ በዓል ላይ አንድ መቶ የሚደርሱ በአካባቢ ጥበቃ ዘርፍ የተሰማሩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሚሳተፉበት የአለም አካባቢ ቀን ኤክስፖ 2015 እንደሚከናወን አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣንና ካሪቡ ኤቨንትስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት በጋራ በሚያዘጋጁት በዚሁ ፕሮግራም ላይ የምድራችን አየር ንብረቷን የሚበክሉ ምርቶችንና አገልግሎቶችን ከመጠቀም እንቆጠብ በሚል ሰፋ ያለ ትምህርታዊ ዝግጅቶች እንደሚኖሩትም ተገልጿል፡፡ በዚህ ዝግጅት ላይ ምድራችንና አየር ንብረቷን የማይበክሉ (Eco frindely) የሆኑ ምርቶችንና አገልግሎቶችን የሚያቀርቡ የግሉ ዘርፍ ተቋማት መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ባለ ድርሻ መንግስታዊ የሆኑ አካላት እንዲሳተፉም አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

Read 1176 times