Saturday, 13 May 2023 20:14

“የመሐረቡ ምስጢር” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በደራሲ እታለም እሸቴ የተጻፈው “የመሐረቡ ምስጢር” የተሰኘ ረዥም ልብወለድ መጽሐፍ ለንባብ የበቃ ሲሆን፤ በመጪው ሳምንት ቅዳሜ ግንቦት 12 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 4 ሰዓት ጀምሮ  በሐገር ፍቅር ቴአትር ቤት እንደሚመረቅ ታውቋል፡፡
በፖለቲካዊ ስላቅ ሥራዎቹ የሚታወቀው ሃማ ቱማ በመጽሐፉ ጀርባ ላይ ባሰፈረው አስተያየት፤ “ ---እኔ እንደ እታለም የረዥም ልብወለድ ታሪኮችን ጽፌ ለማቅረብ አልቻልኩም፡፡ እታለም ተራቀቅሁ፣ ከበድኩ፣ ተመጻደቅኹ በማይል ቋንቋ ከሦስት መቶ በላይ ገጾችን የሚያልፍና ከብዙኃኑ ህይወት ጋር የተሳሰረ ትረካን አስለምዳናለች፡፡ የተፈናቃዮችን ኑሮም እንኖረው ዘንድ በሚታመኑ ገጸባህርያት አማካኝነት አቅርባልናለች፡፡ --- እታለም ከዘመናችን የረዥም ልብወለድ ደራሲዎች አንዷና መነበብም ያለባት ናት እላለሁ፡፡”  ብሏል፡፡ ደራሲዋ ከዚህ ቀደም “ምንዳ” (2001 ዓ.ም)፣ “ህልመኛዋ እናት” (2004 ዓ.ም) ፣ “ተፈናቃይ ፍቅር” (2008 ዓ.ም) የተሰኙ ረዥም ልብወለድ መጻሕፍትን ለአንባቢያን አድርሳለች፡፡



Read 1036 times