Saturday, 03 June 2023 12:03

ቴክኖ ሞባይል ፋንተም ሺ ፎልድ ዘመናዊ ሞዴል ስልክ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  ቴክኖ ሞባይል ዓለማችን የደረሰበት ሞባይል የቴክኖሎጂ ደረጃ ያሳያል የተባለለትን የፋንተም ቪፎልድ (Phantum V told) ሞባይሉን ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ፡፡በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም በተዘጋጀው ስነስርዓት ላይ የቴክኖ ሞባይ ብራንድ ማኔጀር አቶ ኤሊክ እንደተናገሩት ኩባንያው እጅግ ዘመናዊውን የፋንተም ቪ ፎልድ ሞባይል ለገበያ ከሚያቀርብባቸው ውስን ሀገራት መካከል አንዷ ኢትዮጵያ መሆኗ ይህም በአፍሪካ የሞባይል ኢንዱስትሪ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው ብለዋል::ይህ የሚታጠፍ የሞባይል ስልክ ቴክኖሎጂ በመያዝ የተመረተው ፋንታሞ ቪ ቮልድ ሲዘረጋ ባለ 7.85 ኢንች ሰፊ ስክሪን ያለውና በባለ 5 ሌንስ ሲስተም የሚተገበር ካሜራን በመጠቀም ከፍተኛ ጥራት ያላቸው ምስሎችን የማንሳት አቅም ያለው ነው ተብሏል፡፡ባለ 256 ጂቢ ሚሞሪ እና 12 ጂቢ ራም ያለው ይኸው ዘመናዊ ስልክ የሞባይል ስልክን በመጠቀም የተለያዩ ስራዎችን ለሚሰሩ ባለሙያዎች ተመራጭ እንደሆነ ተገልጿል፡፡በአዲስ አበባ ከተማ ጎሮ አካባቢ የሚገኘው የኢትዮ አይሲቲ ፓርክ ውስጥ ያስገነባውን ለአገራችን የመጀመሪያ የሆነውን ዘመናዊ ፋብሪካ በመጠቀም ቴክኖ ሞባይል ላለፉት ዓመታ የተለያዩ አይነትና አገልግሎት ያላቸውን የስልክ ምርቶች በመገጣጠም ለገበያ ሲያቀርብ የቆየ መሆኑ ይታወቃል፡፡


Read 730 times