Tuesday, 01 September 2026 13:30

በአመት 9.1 ቢ. ዶላር ገቢ ባስገኘው አየር መንገዳችን እንኮራለን

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስራ አስፈጻሚ የኡጋንዳ አየር መንገድ ስራ አስፈጻሚ ሆነዋል።
.
አቶ ግርማ ዋቄ ሊፈርስ የደረሰውን አየር መንገድ እንዲያቀኑ ነው ከፍተኛ ሀላፊነት የተጣለባቸው።
????????
ታዲያ ከሰሞኑ ለኡጋንዳ ፓርላማ ሪፖርት ሲያቀርቡ ነበር: ከፍተኛ ውዝግብ ያስነሳ ሪፖርት ነው ያቀረቡት። አቶ ግርማ አየር መንገዱ በሙስና የተነሳ መበስበሱን ገልፀዋል። ኡጋንዳ አየር መንገድ ካሉት 8 አውሮፕላኖች ውስጥ 2ቱ ብቻ እንደሚሰሩ አሳውቀው፤ አየር መንገዱ አደጋ ላይ መሆኑን አቀረቡ።

የኡጋንዳ ፓርላማ "መቼ ነው ከክስረት ወጥተን ማትረፍ የምንጀምረው?" ብሎ በጉጉት ሲጠይቅ አቶ ግርማ "እስከ 2033 ትርፍ የሚባል ነገር አይታሰብም፤ እቅጩን እወቁት" አሉ።
????????
ይህንን ስንሰማ በአመት 9.1 ቢሊየን ዶላር ገቢ ባስገኘው Ethiopian Airlines /የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንኮራለን ስሙንም ከፍ በኩራት እናደርጋለን።

በአመታቶች ውስጥ የስራ አስፈጻሚዎቹ ስልታዊ አመራር፤ የሰፋተኞቹ ታታሪነት እና የመንግስታት ድጋፍ ባበረከቱት አስተዋጽኦ አየር መንገዳችን ከአለም አቀፍ ስመጥር አየር መንገዶች አንዱ ሆኗል።

ዌል እንግዲህ
ባለበት የሚፀና በርትቶ የቆየ ነውና አየር መንገዱ በብርታቱ እንዲቀጥል የሚስተዋሉ የመንገደኞች መጎሳቆል፤ የሻንጣ መጥፋት፤ የሰራተኞች በሙስና መጠመድ፤ የሚታወቅበት hospitality መቀነስ ሊሰራባቸው ይገባል።

Zemelak Endrias-

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

Read 9174 times