ወጣትና አንጋፋ ገጣሚያን በሙዚቃ እየታጀቡ ግጥሞች የሚያቀርቡበት “ግጥምን በጃዝ” ፕሮግራም የፊታችን ረቡዕ ከምሽቱ 12 ጀምሮ እንደሚቀርብ አዘጋጆቹ አስታወቁ፡፡ በራስ ሆቴል ትልቁ አዳራሽ በሚቀርበው ዝግጅት ላይ አንጋፋዋ አርቲስት ሙሉአለም ታደሰ የትያትር ቅንጭብ የምታቀርብ ሲሆን አርቲስት አለማየሁ ታደሰ፣ ሜሮን ጌትነት፣ ምንተስኖት ማሞ፣ ምስራቅ ተረፈ፣ ደምሰው መርሻ፣ በኃይሉ ገብረመድህን ደግሞ የግጥም፣ የወግ እና የዲስኩር ሥራዎቻቸውን ለታዳሚዎች ያቀርባሉ፡፡ የዝግጅቱ መግቢያ ዋጋ 50 ብር እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡