በአበባ ግርማይ ወልደ ሥላሴ የተፃፈው “መውስቦ” የትግርኛ ልቦለድ መፅሐፍ ለንባብ የበቃ ሲሆን በመጪው ረቡዕ አዲስ አበባ በሚገኘው ራስ ሆቴል ከቀኑ 10፡30 እንደሚመረቅ ፀሐፊዋ አስታወቁ፡፡ መጽሐፉ ነሐሴ 15 ቀን ሊመረቅ ታስቦ የነበረ ቢሆንም በእለቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በማረፋቸው ምርቃቱ ተሠርዟል፡፡ የዛሬ ሁለት ወር በመቀሌው “ሚላኖ ሆቴል” የተመረቀውና በድጋሚ በራስ ሆቴል የሚመረቀው የትግርኛ ልቦለድ፤ 200 ገፆች ያሉት ሲሆን ለሀገር ውስጥ በ40 ብር ለውጭ ሐገራት ደግሞ በ8 ዶላር እየተሸጠ ነው፡፡