Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Print this page
Saturday, 17 November 2012 12:16

ዓመታዊው የአውሮፓ ፊልም ፌስቲቫል ተጀመረ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ላለፉት አስር ዓመታት በየዓመቱ በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የአውሮፓ ፊልም ፌስቲቫል የዘንድሮ ዝግጅቱን ማቅረብ ጀመረ፡፡ በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሴ፣ በጣሊያን የባህል ተቋም እና በጎተ የጀርመን የባህል ተቋም እየቀረቡ ያሉት ፊልሞች ከተለያዩ የአውሮፓ ሐገራት የተውጣጡ ሲሆኑ በነፃ ለሕዝብ እየቀረቡ ናቸው፡፡ባለፈው ሰኞ “The Entrepenur” የተሰኘ የጣሊያንን ፊልም በጣሊያን የባህል ተቋም በማሳየት የተጀመረው ፌስቲቫሉ፤ የፖላንድ፣ የፊንላንድ፣ የፈረንሳይና የዴንማርክ ፊልሞች ያሳየ ሲሆን ዛሬ በ11 እና በ1 ሰዓት የአየርላንድ እና የኔዘርላንድ ፊልሞች በጣሊያን የባህል ተቋም ያሳያል፡፡ 

ዝግጅቱ ነገ በተመሳሳይ ስፍራ “Beneath Her Window” የተሰኘ የስሎቬንያ ፊልም፣ ሰኞ የፖርቱጋል ፊልም በጎተ፣ ማክሰኞ የቼክ ፊልም በአሊያንስ፣ ረቡዕ የቤልጂየም ፊልም በጎተ፣ ሐሙስ የስፔን ፊልም በአሊያንስ፣ ረቡዕ የቤልጂየም ፊልም በጎተ፣ ሐሙስ የስፔን ፊልም በአሊያንስ፣ አርብ የቡልጋሪያ ፊልም በጣሊያን የባህል ተቋም እና ቅዳሜ የጀርመን ፊልም በጎተ ያሳያል፡፡ ፌስቲቫሉ የሚዘጋው የነገ ሳምንት እሁድ “The Deep Blue Sea” በተሰኘ የእንግሊዝ ፊልም በጣሊያን የባህል ተቋም ነው፡፡

=====================================

“ስኬታማ የጥናት ዘዴዎች” ለንባብ በቃ
በፈተና ዝግጅት፣ በአጠናን እና ተመሳሳይ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮረው “ስኬታማ የጥናት ዘዴዎች” መጽሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ በብሩክ ሙሉነህ የተዘጋጀው መጽሐፍ ማጣቀሻዎቹን ሙሉ ለሙሉ በድረገፅ መረጃዎች ላይ መስርቷል፡፡ 108 ገፆች ያሉት መጽሐፍ በበረከት ማተሚያ የታተመ ሲሆን ዋጋው 30.50 ብር ነው፡፡ በተያያዘም

Read 2629 times

Latest from