ወ/ሮ የውብማር ከታቃዋሚ ፓርቲዎች አመራር አባላት አንዱ የሆኑትና የቀድሞው የሕወሓት ታጋይ አቶ ገብሩ አስራት ባለቤት ናቸው፡፡
========================================
ሀ-ግዕዝ” ፊልም ሰኞ ይመረቃል
በሀሁ ፊልም ፕሮዳክሽን ተሰርቶ በሪች ፊልም ፕሮዳክሽን የሚቀርበው “ሀ-ግዕዝ” የ92 ደቂቃ ፊልም የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 11 ሰዓት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር እንደሚመረቅ አዘጋጆቹ አስታወቁ፡፡ በዚህ በማህበራዊ ሕይወት ዙሪያ በሚያጠነጥን ፊልም ላይ ገነት ንጋቱ፣ ፍቃዱ ከበደ ማሞ፣ ሔለን በድሉ፣ ተረፈ ለማ፣ መኮንን ላእከ፣ ባህሬን ከድር፣ ያሬድ ዘኪሮስ፣ በሱፍቃድ ታዬ፣ ራሄል ዳሩንዳ ዘላለም ካሳዬ፣ አበበ ባልቻና ሌሎችም ይተውናሉ፡፡ ፊልሙን ለመስራት ሰባት ወራት የፈጀ ሲሆን ነገ ከ8 እስከ 12 ሰዓት በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች እንደሚታይና ሰኖ እንደሚመረቅ ለማወቅ ተችሏል፡፡