ከጥቅምት 28 ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲካሄድ የቆየው “ከለርስ ኦፍ ዘ ናይል” ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል በአስር ዘርፎች ሽልማት በመስጠት ባለፈው እሁድ ምሽት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር ተጠናቀቀ፡፡ ብሉ ናይል ፊልም እና ቴሌቪዥን አካዳሚ ከኢትዮጵያ ፊልም ሰሪዎች ማህበር ጋር ባዘጋጁት ፌስቲቫል፤ 58 ፊልሞች ተሳትፈው ሽልማቱ ተሰጥቷል፡፡ በተለያዩ ዘጠኝ ዘርፎች ከስድስት የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ባለሙያዎች እና ፊልሞች “ምርጥ” በመባል ዋንጫ ሲሸለሙ የፌስቲቫሉን ትልቁን ሽልማት “ዘ ግራንድ ናይል አዋርድ“ የናይጄርያው ፊልም አሸንፏል፡፡