Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Monday, 08 August 2011 09:37

..ማሕሙድ ጋ ጠብቂኝ.. የተሰኘው ወግ በመጽሐፍ ታተመ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በቀድሞው ..የአዲስ ነገር.. ጋዜጠኛ መሐመድ ሰልማን የቀረቡ ልዩ ልዩ ወጎችና የጉዞ ማስታወሻዎችን የያዘ መጽሐፍ በቀጣዩ ሳምንት ለንባብ ይበቃል፡፡ ..ፒያሳ፣ ማሕሙድ ጋ ጠብቂኝ.. የሚል ርዕስ የተሰጠው ይህ መጽሕፍ በአመዛኙ በቀድሞው አዲስ ነገር ጋዜጣ ላይ ቀርበው በስፋት የተነበቡ ወጎችና የጉዞ ማስታወሻዎችን ከአዳዲስ ስራዎች ጋር የያዘ ስብስብ ስራ ሲሆን 200 ገጾች አሉት፡፡

ጋዜጠኛ መሐመድ ሰልማን በማህበራዊ አምድ ስር በ..አዲስ ነገር.. ጋዜጣና ድረ-ገጽ ላይ ተነባቢ የነበሩ ከ15 በላይ ጽሁፎችን አሰባስቦ ነው ለንባብ ያቀረበው፡፡ ..ማሕሙድ ጋ ጠብቂኝ.. የተሰኘው ተራኪ ወግ የአዲስ አበባዋን ፒያሳ ህይወትና ገጽታ የሚያስቃኝ ጽሁፍ ሲሆን ከዚህ ቀደም በሸገር ሬድዮና በቪኦኤ በከፊል የቀረበ ስራ ነው፡፡ ..ማሕሙድ ጋ ጠብቂኝ.. መጽሐፍ የተዘጋጀው በአሮን አሳታሚ እንደሆነ ታውቋል፡፡

 

Read 4355 times Last modified on Monday, 08 August 2011 09:39