የኢትዮጵያ ሴት ደራስያን ማህበር ነገ ጧት በብሔራዊ ትያትር ስቱዲዮ አዳራሽ የአመራር አባላት እንደሚመርጥ አሳወቀ፡፡ በደራሲ የምወድሽ በቀለ ፕሬዚዳንትነት የሚመራው የአሁኑ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አመራር ለሁለተኛ ጊዜ መወዳደር እንደሚችልና የተጓደሉ አመራሮችን ለመምረጥም መታቀዱን ከማህበሩ የተገኘው መግለጫ ያስረዳል፡፡ ከምርጫው ሌላ መደበኛ የኪነጥበብ ዝግጅት እንደሚኖርም ማወቅ ተችሏል፡፡
የኢትዮጵያ ሴት ደራስያን ማህበር ነገ ጧት በብሔራዊ ትያትር ስቱዲዮ አዳራሽ የአመራር አባላት እንደሚመርጥ አሳወቀ፡፡ በደራሲ የምወድሽ በቀለ ፕሬዚዳንትነት የሚመራው የአሁኑ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አመራር ለሁለተኛ ጊዜ መወዳደር እንደሚችልና የተጓደሉ አመራሮችን ለመምረጥም መታቀዱን ከማህበሩ የተገኘው መግለጫ ያስረዳል፡፡ ከምርጫው ሌላ መደበኛ የኪነጥበብ ዝግጅት እንደሚኖርም ማወቅ ተችሏል፡፡