Monday, 08 August 2011 14:35

መጥኔ ፕሬስና ኳስ!

Written by  ነ.መ
Rate this item
(0 votes)

መጥኔ ፕሬስና ኳስ
የሀገር ህመምና ፈውስ
ሁሉም የልቡ እስኪደርስ!
መጥኔ ፕሬስና ኳስ
ሁለቱም የነፃነት ዋስ
ባንድ ፊት ያገር እስትንፋስ
ባንድ ፊት የመዝናኛ ዳስ
ልደቱን ከምጡ ሚወርስ
ትግሉን በድል እሚክስ
የህይወት መልክና ገበር፣ ይሄው ነው ፕሬስና ኳስ
የዓለም ተፃራሪ ፀባይ፣ የሀገር ህመምና ፈውስ፡፡
አሴዋ
ዛሬም እየዋ
ገባልህ የዋንጫ ዋ!
ትግልህ የተጫዋች እልክ
ድልህ የተመልካች ልክ፡፡
ይሄዋ አሴ ያልከው ሆነ
አድማስህ ድሉን ዘገነ
ፕሬስና ኳስ ተካነ
በእጅ የተፃፈው ቃል ሁሉ፣ በግር የተፃፈ ወርቅ ሆነ!!
..ህዝብ ሲያውቅ እኔም አውቅ.. እንዳልክ፤
እንካ ዋንጫውን ተረከብ፣ ሲያሸንፍም አንተ አሸነፍክ!!
ዛሬ ህልምህን ዕውን አረክ
ደግ አረክ! አሴ ደግ አረክ!
አሴዋ
ዛሬም እየዋ
ገባልህ የዋንጫ ዋ!

ተረካቢህ አያሳፍር፣ ድፍን - ታታሪ ጨዋ፡፡
ተንቀለቀለ ቀንዲሉ፣ ያድማስህ ድምር ደመራ
ጋመ ንብርብሩ ፍም፣ አንተኑ በእሳት ሊጠራ!
ቀን ይጠብቃል እንጂ፣ ድል የትጉህ እጅ ነው
ወትሮም ካድማስ ጎህ ይቀዳል፣ ጎርፍም የዥረት ጅራፍ ነው
ከእያንዳንዱ ድል ጀርባ፣ አንዳንድ ጀግና ካለ
አንተ ነህ አሴ ልባሙ፣ ህልምህ በድል የተኳለ!
ተስፋህ ንፍ አያቅምና፣ ገና ይበራል ቀንዲሉ
አድማስህ ኬላ የለውም፣ ገና ይሰፋል ፀዳሉ፡፡
..ህዝብ ሲያውቅ እኔም አውቅ.. እንዳልክ
እንካ ዋንጫውን ተረከብ፣ ሲያሸንፍም አንተ አሸነፍክ!!
(ለአሴዋ ለአዲስ አድማስ ተጫዋቾችና ድል ለሚገባቸው ሁሉ)
ሐምሌ 28 2003 ዓ.ም

 

የ2003 የሩጫና እግር ኳስ ድሎች መታሰቢያነት ለአሰፋ ጐሳዬ ሆነ

 

Read 3767 times Last modified on Monday, 08 August 2011 15:38