በወህኒ ቆይታው ዝነኞች ገበናቸውን እንዲሸሽግላቸው፣ የፍትህ አካላት ደግሞ እንዲያጋልጥ በሚያደርጉት ጉትጎታ መቸገሩን ከኒውስዊክ ጋር ባደረገው ሰፊ ቃለምልልስ የተናገረው ፔሊካኒ፤ ትላልቅ የሚዲያ ተቋማት በእጁ ያሉትን ምስጥራዊ መረጃዎች እንዲሰጣቸው ደጅ ጥናት እንዳበዙ ገልል፡፡ ከፔሊካን ደንበኞች ከነበሩት መካከል ሸዋዚንገር፣ ማዶና፣ ማይክል ጃክሰንና ሌሎችም ይገኙበታል””በወህኒ ቤት በየቀኑ በመቶዎች በሚቆጠሩ ሰዎች እየተከበበ ቢሆንም የህይወት ታሪኩን የያዘ መጽሐፍ ለማዘጋጀት ጥረት እያደረገ መሆኑን የገለፀው አንቶኒዮ ፔሊካኒ፤ የተወሰነበት የእስር ቅጣት ተገቢ እንዳልሆነ የሚገልጽ ባለ 86 ገ ደብዳቤ አዘጋጅቶ ፍ/ቤት ይግባኝ ብሏል፡፡ ይግባኙ ተቀባይነት አግኝቶ የተበየነበትን እስር ከመጨረሱ ስድስት ዓመት ቀደም ብሎ በ2013 እ.ኤ.አ ላይ በነፃ እለቀቃለሁ የሚል ተስፋ እንዳለው ፔሊካን ተናግሯል፡፡ የ67 ዓመቱ ፔሊካኒ የፍርድ ብይን ያልተሰጠባቸው ከ30 በላይ የፍትሐብሔር ክሶች እንዳሉበትም ለማወቅ ተችሏል፡፡