አፕል አይክላውድ (icloud) የተባለውን የሙዚቃ ስቶር ከፍቶ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ትንሽ ሰንበትበት ያለ ሲሆን ብላክቤሪ ደግሞ እ.አ.አ. ከመስከረም 6 በኋላ ይጀምራል፡፡
የብላክቤሪ ሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች ኩባንያው አዲስ ከሚከፍተው ውስጥ (ክሊፕ አልባ) ሙዚቃዎችን እና ሌሎች ፋይሎችን ቀድተው መውሰድ የሚችሉ ሲሆን የተለያዩ የሙዚቃ አፕሊኬሽኖችንም ማግኘት ይችላሉ፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ አዲሱ የብላክቤሪ ኔትዎርኪንግ ሲስተም ፈጣን እና በዚያ ለሚደረጉ የተለያዩ የመረጃ ልውውጦች የሚጠይቀው ወጪም በጣም አነስተኛ በመሆኑ በተጠቃሚው ዘንድ ተቀባይነትን ሊያስገኝለት እንደሚችል የተነገረ ሲሆን በአዲሱ ቨርዥን ተጠቃሚዎች በአነስተኛ ወጪ የተለያዩ መልእክቶችን ከመቀባበል ባሻገር ዜናዎችን እና የቪዲዮ ጌም አፕሊኬሽኖችን ሁሉ ማግኘት ይችላሉ፡፡