Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Print this page
Saturday, 03 September 2011 12:50

የኢትዮጵያ ሙዚቃ የዓለም ገበያን እየተቀላቀለ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

አዲስ አኩስቲክ የሙዚቃ ቡድን ትውስታ (Remembrance) የተሰኘውን አዲስ የሙዚቃ አልበም ለገበያ ማብቃቱ ታወቀ፡፡ ከኢትዮጲክስ ተከታታይ የሙዚቃ አልበሞች ስኬታማ ገበያ b|§ ተሻሽለውና በአዲስ መልክ ተቀናብረው ለዓለም ገበያ የቀረቡ ኢትዮጵያዊ ዘፈኖች በዓለም አቀፍ ደረጃ ፋሽን እየሆኑ መምጣታቸውን ዘ ጋርድያን ሰሞኑን ዘግቦታል፡፡ በዓለም ዙሪያ ከ30 በላይ የሙዚቃ ባንዶች በድሮ የኢትዮጵያ ዘፈኖች ዜማ ሙዚቃዎቻቻውን እየሠሩ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡

በአዲስ አኩስቲክ ፕሮጀክት የተሰራው አዲሱ አልበም ትውስታ ለሁለት ዓመታት ዝግጅት ሲደረግበት ቆይቷል ያለው የዴይሊ ቴሌግራፍ ቅኝት ዋጋው 20.40 ዩሮ መሆኑን አመልክቷል፡፡ በ50ዎቹ እና 60ዎቹ የተሠሩ ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቃዎች እንደገና በዘመናዊና በባህላዊ የሙዚቃ መሣሪያዎችና ቅኝቶች የተዘጋጁበት አልበም በአስደናቂ የጥራት ደረጃ መሠራቱን ..ዘ ጋርዲያን.. ዘግቧል፡፡ የአዲስ አኩስቲክ ፕሮጀክትን ጊታሪስቱ እና የአኮርዲዮን መሣሪያ ተጫዋች ግሩም መዝሙር መስርቶታል፡፡ በትውስታ አልበም ላይ በሙዚቃ ቅንብር ግሩም መዝሙር ንቁ ተሳትፎ ያደረገ ሲሆን ሄኖክ ተመስገን በደብል ቤዝ ጊታር፣ ናትናኤል ተሰማ በድራም፣ አየለ ማሞ በማንዶሊን፣ መሰለ ለገሠ በከበሮ ተጫወችነት ከተሳተፉት መካከል ይገኙበታል፡፡

 

Read 3707 times Last modified on Tuesday, 06 September 2011 14:13

Latest from