Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 10 September 2011 12:05

ወላጅ መጽናኛ!

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ወላጅ መጽናኛ!
አንድ ዘመን ሄደ፣
አንድ ዘመን መጣ፣
በአንድ አመት አረጀሁ፣
በአንድ አመት ጐረመስኩ፣
በራሴ ሲያልፍብኝ፣
በልጄ እየደረስኩ፡፡
እምሻው ገ/ዮሐንስ
ሰው፣ ጊዜና ወርቅ!
በትውልድ እድገቱ
ኑሮውና ሞቱ
አድርጐ እንደ ጥላው
በእለትና ወራት
አመታት፣ ዘመናት
ቀምሮ እያሰላው
እንደ አፈር ቆንጥሮ
እንደ አፈር አንጥሮ
የሰው ልጅ ባይቀባው
የክብርን ቀለም፣
ከንቱ ውዳቂ እንጅ
በድን ለዘላለም
በሰው ካልተለካ
ጊዜ ወርቅ አይደለም፡፡  
እምሻው ገ/ዮሐንስ

Read 5663 times Last modified on Saturday, 10 September 2011 12:07