Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 10 September 2011 13:45

..የሥልጣኔና የጥጋብ ዘመን እንዲሆን ምኞቴ ነው..

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ካለፉት ጊዜያት አንፃር 2003 ስገመግመው ሥራዎች በጥራትና በብዛት እየተስፋፉ ነው፡፡ ሕዝቡ ትያትሮችን እየተመለከተ እና እየወደደ  መምጣቱ በጣም የሚያስደስት ነገር ነው፡፡ በእኔ በኩል በ2003 ዓ.ም በድርጅቴ የሠራሁት ..የሚስት ያለህ.. ትያትርን ነው፡፡ ከየካቲት ወር ጀምሮ በብሔራዊ ቲያትር እየታየ ነው፡፡ በፊልም ደረጃ ደግሞ ..ሔሮሺማ.. ላይ ሠርቻለሁ፡፡ ይሄንን በማድረጌ ለጥበቡ እድገት አስተዋጽኦ አበርክቻለሁ እላለሁ፡፡ በጽሑፍና በትወና የምሳተፍባቸው ሥራዎች ደግሞ በ2004 ይቀጥላሉ፡፡

በ2003 ዓ.ም ካየሁት አስገራሚ ክስተት የአረቡ ዓለም ንቅናቄ ነው፡፡ ነፃነትን ማግኘት ደስ የሚል ነው፡፡ በጣም ያስደሰተኝ ደግሞ ግብጽ ውስጥ ከአመፁ በኋላ ከተማዋን ያፀዱት ነገር ከልቤ ቀርቷል፡፡ በዓለም ላይ ያሉ መጽሐፍቶችን በአገራችን እንደልብ ማግኘታችን ሌላው ደስ እንዲለኝ ያደረገ ነገር ነው፡፡ በአገራችን ተከስቷል የምለው አስቸጋሪ ነገር የኑሮ ውድነት ነው፡፡ ሰው እንዴት እንደሚኖር እየተገረምኩ ያለሁበት ነገር ነው፡፡ እግዚአብሔር የተሻለ ቀን እንዲያመጣ እናፍቃለሁ፡፡ ለምግብ የሚሆኑ ነገሮችን ለመግዛት መሠለፍ አስቸጋሪ ነገር ነው፡፡ ወዴት እየሄድን እንደሆነ አስባለሁ፡፡
በ2004 ዓ.ም ኢትዮጵያ የጥጋብ ዓመት፣ የሥራ ውጤታማነት የሚታይበት፤ ወጣቱ የሥራ ፈጠራና የሥራ ተነሳሽነትን የሚያሳይበት ቀናነት የነገሰበት የሥልጣኔ፣ የጥጋብ ዘመን እንዲሆን ምኞቴ ነው፡፡
አዜብ ወርቁ
ደራሲና ተዋናይ

 

Read 3645 times Last modified on Saturday, 10 September 2011 13:47