በ2003 ዓ.ም ካየሁት አስገራሚ ክስተት የአረቡ ዓለም ንቅናቄ ነው፡፡ ነፃነትን ማግኘት ደስ የሚል ነው፡፡ በጣም ያስደሰተኝ ደግሞ ግብጽ ውስጥ ከአመፁ በኋላ ከተማዋን ያፀዱት ነገር ከልቤ ቀርቷል፡፡ በዓለም ላይ ያሉ መጽሐፍቶችን በአገራችን እንደልብ ማግኘታችን ሌላው ደስ እንዲለኝ ያደረገ ነገር ነው፡፡ በአገራችን ተከስቷል የምለው አስቸጋሪ ነገር የኑሮ ውድነት ነው፡፡ ሰው እንዴት እንደሚኖር እየተገረምኩ ያለሁበት ነገር ነው፡፡ እግዚአብሔር የተሻለ ቀን እንዲያመጣ እናፍቃለሁ፡፡ ለምግብ የሚሆኑ ነገሮችን ለመግዛት መሠለፍ አስቸጋሪ ነገር ነው፡፡ ወዴት እየሄድን እንደሆነ አስባለሁ፡፡
በ2004 ዓ.ም ኢትዮጵያ የጥጋብ ዓመት፣ የሥራ ውጤታማነት የሚታይበት፤ ወጣቱ የሥራ ፈጠራና የሥራ ተነሳሽነትን የሚያሳይበት ቀናነት የነገሰበት የሥልጣኔ፣ የጥጋብ ዘመን እንዲሆን ምኞቴ ነው፡፡
አዜብ ወርቁ
ደራሲና ተዋናይ