Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Print this page
Saturday, 10 September 2011 13:55

..ሥራ አጥ የማይኖርባት አገር እመኛለሁ..

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የሙዚቃ ሙያው አድጓል፤ ጥሩ ባንዶች እየተቋቋሙ ነው፡፡ ቀደም ሲል በኪቦርድ ብቻ ይሠራ የነበረው አሁን  በቡድን በደንብ የሚጫወቱትን ሳይ ደስ ይለኛል፡፡ ገና ብዙ ነገሮች ቢቀሩትም መንግሥት በቅጂ መብት ዙሪያ ያደረገው ጥበቃ ደስ ይለኛል፡፡ እኔ በግሌ ለሞያው አስተዋጽኦ እያደረኩ ነው፡፡ ለአዲሱ ዓመት ..የበረሀ ስደተኛ.. የሚል ነጠላ ዜማ ለቅቄያለሁ፡፡ አሁን ደግሞ ቴዲ አፍሮ ተጨምሮበት ዘፈኑን አሳድገን ክራር እና ማሲንቆ ጨምረን እንዲያስጨፍር አድርገን፣ በቆንጆ ሁኔታ ሁለት ሆነን ሠርተነዋል፡፡ ለብዙ ዘመን ሁለት ሰው መሥራት ቆሞ ነበር፤ አሁን ግን ከታላቁ ከማከብረው ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ ጋር ሠርቻለሁ፡፡ በ2003 ዓ.ም በኖርንበት አሜሪካ የደረሰው የተፈጥሮ አደጋ፤ ባልተለመደበት በቨርጂኒያና በዲሲ መድረሱ ያስፈራል፡፡ በሀገራችን የሚታየው የኑሮ ውድነትና ሥራ አጥነት በጣም ያስከፋል፡፡ አስደሳቹ በአገራችን መንገድ እና በርካታ ቤቶች መሠራታቸው ነው፡፡
ኢትዮጵያ እግዚአብሔር የቀደሳት፤ ሕዝቡ አብሮ ተዛዝሎ እና ተቃቅፎ የሚኖርባት አገር ናት፡፡ እኔም በ2004 ዓ.ም ኢትዮጵያ ስራ አጥ የማይኖርባት፤ የትምህርት ቤት ጥራት የሚያድግባት፤ የተማረ ሥራ ሠርቶ የሚኖርባት አገር እንድሆን እመኝላታለሁ፡፡
ኩኩ ሰብስቤ
ድምፃዊ

Read 5276 times

Latest from