በአዲስ አበባና በኒውዴልሂ በ2000 ተማሪዎች መካከል በተካሄደ ውድድር ያሸነፉ ስድስት ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በአሜሪካ ፍሎሪዳ ግዛት የሚገኘውን ናሳ የጠፈር ምርምር ማዕከል ጎበኙ፡፡ ተማሪዎች ከሕዳር 16 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ለስድስት ቀናት በማዕከሉ ባደረጉት ጉብኝት የጠፈር መንኩራኩሮችን እና የናሳ ቤተመዘክርን እንደጐበኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡